1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቦስተን አሸባሪዎችና የፖሊስ ክትትል ፣

ዓርብ፣ ሚያዝያ 11 2005

በዩናይትድ ስቴትስ ቦስተን ከተማ የፈንጂ ጥቃት ከተጠርጣሪዎች አንዱ መገደሉን አንደኛዉን ፍለጋዉ መቀጠሉን ፖሊስ አስታወቀ። ዛሬ የወጡ ዘገባዎች እንደሚሉት ከተጠርጣሪዎቹ አንዱ በጥይት ተመትቶ ሃኪም ቤት ሲደርስ ህይወቱ አልፏል።

https://p.dw.com/p/18JfX
ምስል Getty Images

የሀገሪቱ ፌደራል የምርመራ ቢሮ FBI ትናንት በሰጠዉ መግለጫ ከሰኞ ዕለቱ የቦስተን ማራቶን ፍንዳታ ጋ በተያያዘ ሁለት ሰዎች መጠርጠራቸዉን ጠቁሟል። ከቅኝት ካሜራዎች የታየዉ ሌላኛዉ ነጭ የቤዝቦል ተጫዋች ኮፍያ እንዳደረገ የተገለፀዉ ተጠርጣሪ ግን አምልጧል። ተጠርጣሪዎቹ የቼቺንያ ዜጎች መሆናቸዉ የተገለፀ ሲሆን ያመለጠዉ የ19 ዓመት ወጣት ቦስተን አቅራቢያ ካምብሪጅ ኗሪ እንደነበር አሶሲየትድ ፕረስ ዘግቧል። የቦስተን ፖሊስ ኮሚሽነር ኤድ ዳቪስ፤
«አሁን በመፈለግ ላይ የምንገኘዉ ተጠርጣሪ ቁጥር ሁለት በሚል የተገለፀዉን ሲሆን ባለነጭ ኮፍያዉ ግለሰብ በሰኞ ዕለቱ የቦስተን ማራቶን የቦምብ ጥቃት እጁ እንዳለ ይጠረጠራል።»

USA Boston Marathon Anschläge Verdächtiger
ምስል picture alliance / ZUMAPRESS


ከዚህም ሌላ ተጠርጣሪዎቹን በማደን ላይ ከነበሩ አንድ ፖሊስ መገደሉና አንድ ሌላ መቁሰሉም ተገልጿል። አያይዞም ፖሊስ የቦስተን ከተማ ኗሪዎች የሚታደነዉ ተጠርጣሪ አደገኛና መሳሪያ ሳይታጠቅ እንዳልቀረ በመግለፅ ከቤታቸዉ እንዳይወጡ አሳስቧል። ኗሪዎች በራቸዉን እንዲቆልፉና ለማያዉቁት ሰዉ እንዳይከፍቱም አስጠንቅቋል። የሰኞ ዕለቱ የቦምብ ጥቃት እስካሁን ለሶስት ሰዎች ህልፈተ ህይወት ምክንያት ሲሆን ቢያንስ አንድ መቶ ሰማንያ ሰዎችን ለጉዳት ዳርጓል። በጥቃቱ የተጎዱትን ለማሰብ ትናንት በቦስተን ከተማ ካቴድራል ዉስጥ በተካሄደዉ ስርዓት ላይ የተገኙት ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ጥቃት አድራሾቹን አድኖ ለፍርድ ማቅረብ የማይቀር መሆኑን አመልክተዋል።
«ይህን ጥቃት ለፈፀሙትም ሆኑ ህዝባችንን ለመጉዳት የሚሞክር ማንም ቢሆን አዎ እናገኛችኋለን። አዎን ይዘን ለፍርድ እናቀርባችኋለን።»


ቦቦስተን ዓመታዊ የማራተን ውድድር የፈንጂ አደጋ ተጥሎ በዛ ያሉ ሰዎች ከቆሰሉና 3 ሰዎች ከሞቱ ወዲህ ፣ ፖሊስ ፣ አደጋ ጣዮችን በቪዲዮና በህዝብ እርዳታ ለማግኘት ያደረገው ጥረት ሌሊቱን ከፊል ውጤት ሳያስገኝለት አልቀረም፤ ከ 2 ቱ ተጠርጣሪዎች መካከል አንደኛው በአውቶሞቢል ለማምለጥ ሲጥር ከፖሊስ ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ተገድሏል። ሌላው አልተያዘም ። መሣሪያ በመታጠቁም በህይወት ሊያዝ መቻሉ ሳያጠራጥር አልቀረም ። የቅርብ ጊዜ መጤዎች ናቸው ስለተባሉት 2 አሸባሪ የአሜሪካ ኑዋሪዎች ፣ የዋሽንግተን ዲ ሲ ውን ዘጋቢአችንን ፣ አበበ ፈለቀን በስልክ አነጋግሬው ነበር።

USA Schießerei MIT Universität Massachusetts Boston Marathon Watertown
ምስል picture-alliance/AP

አበበ ፈለቀ

ተክሌ የኋላ

ሂሩት መለሰ