1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተመድ እና የማሊ ተልዕኮ ጉዳይ

ቅዳሜ፣ ኅዳር 22 2005

የተ,መ,ድ ፀጥታ ምክር ቤት በሰሜናዊ ማሊ አንድ የአፍሪቃ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል የሚሰማራበትን ዉሳኔ እንዲያመቻች የዓለሙ መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ

https://p.dw.com/p/16uBf
Bewaffnete Tuareg-Kämpfer auf ihrem Pick-up; Nordmali am 15.02.2012. Nach dem Sturz von Gaddafi in Libyen ist der Bürgerkrieg in Mali zwischen Tuareg-Rebellen und den Regierungstruppen eskaliert. Fast 130.000 Menschen befinden sich laut UN auf der Flucht. Rund die Hälfte flüchtete ins Ausland, die andere Hälfte sind Binnenflüchtlinge. Durch die bestehende Nahrungsmittelknappheit in der Sahelzone droht eine humanitäre Katastrophe.
ምስል picture-alliance/Ferhat Bouda

የተ,መ,ድ ፀጥታ ምክር ቤት በሰሜናዊ ማሊ አንድ የአፍሪቃ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል የሚሰማራበትን ዉሳኔ እንዲያመቻች የዓለሙ መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ ባንኪሙን ባለፈዉ ረቡዕ ሃሳብ አቅርበዋል። ይሁንና ዋና ፀሃፊዉ ድርጅታቸዉ ለዚሁ በማሊ ይሰማራል በሚባለዉ ተልዕኮ የገንዘብ ርዳታ ማድረግ አለማድረጉን ሳይጠቅሱ ነበር ያለፉት። በማሊ እንዲጀመር የተፈለገዉን የሰላም ተልዕኮ ከሌሎች የተ,መ,ድ ሰላም ማስጠበቅያ ወይም ማስከበርያ ተልዕኮዎች ልዩ የሚያደርገዉ፤ በዉግያ ተግባር ተሳታፊ መሆን መቻሉ መሆኑን የዓለሙ መንግስታት ድርጅት ዲፕሎማቶች ገልጸዋል። የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ፤ እስከ መጭዉ ታህሳስ አጋማሽ ድረስ፤ ይኸዉ የአፍሪቃ ህብረት የሰላም ተልዕኮ በማሊ የሚሰማራበትን ረቂቅ ዉሳኔ  እንዲያወጣ ፈረንሳይ ጠይቃለች።

Innenansicht des Sicherheitsrates der Vereinten Nationen, aufgenommen am 13.07.2011 in New York (USA). Die Debatte dreht sich um das Thema "Empfehlung zur Aufnahme des Südsudan". Foto: Soeren Stache
ምስል picture-alliance/dpa

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሰሜናዊ ማሊን በጠቅላላ፤ ከፅንፈኞቹ አማፅያን ቁጥጥር፤  ነፃ መሆን አለበት በሚለዉ ሃሳብ ላይ ይስማማሉ። ይን ለማሳካትም፤ የምዕራብ አፍሪቃ መንግስታት  የኢኮነሚ ማህበረሰብ በኢንግሊዘኛ ምህፃሩ ECOWAS - 3300 ወታደሮችን ወደ ማሊ ለመላክ ፍላጎቱን ካሳየ ብዙ ወራት አልፈዋል። ለዚሁ የምዕራብ አፍሪቃ መንግስታት  የኢኮነሚ ማህበረሰብ ECOWAS ጦር ፤ ወታደሮች የሚያዋጡት ሀገራት፤ ናይጀሪያ፤ሴኔጋል፤ ኒጀር፤  ቡርኪናፋሶ፤ ጋና ና ቶጎ ናቸዉ። 

አርያም ተክሌ

መስፍን መኮንን 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ