1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተቃዉሞ ሠልፍ በለንደን

ዓርብ፣ መስከረም 3 2006

ዛሬ ለንደን ብሪታንያ ምክር ቤት ፊትለፊት የተሠለፉት የኦሮሞ ተወላጆች እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የሚያደርሰዉ በደል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ነዉ።የብሪታንያ መንግሥት ሠልፈኞቹ «ዜጎቹን ይበድላል» ላሉት ለኢትዮጵያ መንግሥት የሚሠጠዉን ድጋፍ እንዲያቆም ሠልፈኞቹ ጠይቀዋል

https://p.dw.com/p/19hN4
Demo in London, London Old Palace Yard, 13/09/13, Foto: DW/H. Demisse A demonstration against the continued mass arrests, torture and killings of Oromo nationalists, political activists, dissents and innocent civilians by the security forces of the Ethiopian regime.
ምስል DW/H. Demisse

ብሪታንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን የኦሮሞ ተወላጆች የኢትዮጵያ መንግሥት በሐገሪቱ ሕዝብ በተለይም በኦሮሞ ተወላጆች ላይ ይፈፅመዋል ያሉት የሠብአዊ መብት ረገጣ እንዲያቆም በሠላማዊ ሠልፍ ጠየቁ።ዛሬ ለንደን ብሪታንያ ምክር ቤት ፊትለፊት የተሠለፉት የኦሮሞ ተወላጆች እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የሚያደርሰዉ በደል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ነዉ።የብሪታንያ መንግሥት ሠልፈኞቹ «ዜጎቹን ይበድላል» ላሉት ለኢትዮጵያ መንግሥት የሚሠጠዉን ድጋፍ እንዲያቆም ሠልፈኞቹ ጠይቀዋል።ጥያቄያቸዉን ለብሪታያ ዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በደብዳቤ ማመልከታቸዉንም አስታዉቀዋል።የለንደንዋ ወኪላችን ሐና ደምሴ ዝርዝር ዘገባ ልካልናለች።

ሐና ደምሴ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ