1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ኤኮኖሚ

የቱሪዝም ገቢ መጨመሩ

ረቡዕ፣ የካቲት 20 2011

ባለፉት ስድስት ወራት ኢትዮጵያ ከውጭ ሃገራት ሀገር ጎብኚዎች ከአንድ ነጥብ አራት ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። ለጉዳት የተጋለጡ ታሪካዊ ቅርሶችን የመጠገን ሥራም ተጀመረ።

https://p.dw.com/p/3ECrD
Unesco Äthiopien - Ortodoxe Kirceh Lalibela
ምስል Getty Images/AFP/C. de Souza

ለጉዳት የተጋለጡ ታሪካዊ ቅርሶችን የመጠገን ሥራ መጀመሩ

የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኂሩት ካሳው በተለይ ከ DW ጋር ባደረጉት ቃለ-መጠይቅለ በአንዳንድ አካባቢዎች  የሚከሰቱ ግጭቶች  እያደገ በመጣው የአገሪቱ የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ላይ ትጽዕኖ እንዳያስከትል መንግሥት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደመሆነም ተናግረዋል:: በ2011 የበጀት ዓመት ለመጠገን ዕቅድ ከተያዘላቸው ለጉዳት የተጋለጡ የተለያዩ  ባህላዊ እና ታሪካዊ  ቅርሶች መካከል የ 26ቱ የጥገና ሥራ መጀመሩንም ሚኒስትሯአመልክተዋል ::  እንዳልካቸው ፈቃደ ዝርዝሩን አጠናቅሮታል::

 እንዳልካቸው ፈቃደ

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ