የቱኒዝያ ጊዚያዊ ሁኔታ
ሰኞ፣ ሐምሌ 29 2005
አንፃር መንግሥት ቁርጠኛ ርምጃ አልወሰደም በሚል አብዝተው ወቅሰውታል። በቱኒዝያ ባለፉት ጥቂት ጊዚያት ውስጥ አንድ የተቃዋሚ ወገን ፖለቲከኛ ሲገደል ብራሂሚ ሁለተኛው ናቸው። የብራሂሚ ቤተሰቦች እና የፓርቲያቸው አባላት ለግድያው ሳላፊስቶቹን ተጠያቂ አድርገዋል።
የቱኒዝያ ጠቅላይ ሚንስትር አሊ ላራዬድህ መንግሥታቸው ላረፈበት ግፊት እንደማይንበረከክ በመግለጽ የፊታችን ታህሳስ ምርጫ እንደሚደረግ አስታውቀዋል። ብዙ ቱኒዝያውያን መንግሥት ምርጫው ከአምሥት ወራት በኃላ እንዲደርግ መወሰኑ ሂደቶችን የማጓተተ ኣና በሠልጣን የሚቆየበትን ጊዜ ለማራዘም የተከተለው ሥልት አድርገው ተመልክተውታል።
በአሥር ሺህ የሚቆጠሩ ቱኒዝያውያን፣ የሙያ ማህበራት ጭምር ካለፊት ሳምንታት ወዲህ በመዲናይቱ ቱኒስ አደባባይ በመውጣት በኤናሀዳ ፓርቲ አንፃር ተቃዎሞ አሰምተዋል።
በዚሁ ወቅትም ከአክራሪ ሙስሊሞች ጋ ተደጋጋሚ የተፈጠረውን ግጭት ለማብረድ በማሰብ ነበር መንግስት የምርጫውን ዕለት ለ17፣12፣2013 የወሰነው። በዚህ ጊዜ ውስጥ ሕገ መንግሥታዊው ምክር ቤት የምርጫውን ሕግ ያወጣል ተብሎ ይጠበቃል። ይሁንና፣ የኤናሀዳ ፓርቲ ተወካዮች የሚገኙበት ምክር ቤት ከሕዝብ የነበረው መ ልካም ስም እያጣ መሄዱን የምክር ቤቱ እንደራሴ ካሜያስ ክሺሊ ገልጸዋል።
« ሕገ መንግሥታዊ ምክር ቤት ተዓማኒነቱን አጥቶዋል,። ይህ ምክር ቤት አንድመ ተስፋ አይሰጥም።ሕገ መንግሥት ማወጣት አልተሳካለትም በኤኮኖ ሚውም ሆነ በማህበራዊው ዘርፍ አንድ ደህና ውስጥ ማስመዝገብ አልተሳካለትም»
ከምክር ቤቱ ሁለት መቶ አሥራ ሰባት እንደራሴዎች መካከል አንድ ሦሰተኛው ከምክር ቤቱ ርቆዋል። ይህ ቁጥር ከጨመረ ምክር ቤቱ መበተኑ አይቀርም።
በ2011 የቀድሞው ፕሬዚደንት ቤን አሊ ከስልጣን ከተወገዱ ወዲህ የቱኒዝያውያኑ ሕይወት አልተሻሻለም። በአንፃሩ ተበላሽቶዋል። በሀገሪቱ መረጋጋት ተጓድሎዋል፣ ኤኮኖሚ ዕድገት አላሳየም፣ ስራ አጥነት ተስፋፍቶዋል። ቱኒዝያ ከዚህ ወዝግብ ትወጣ ዘንድ የተለያዩት ተቀናቃኝ ኃይላት ባንድነት ምስራት እንደሚጠበቅባቸው በመንግስቱ ውስጥ ከኤናሀዳ ጋ የተጣመረው የግራ ክንፍ ኤታካቶል ፓርቲ አባል መሀመድ ቤኑር ገልጸዋል።
«የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ያስፈልገናል። በዚሁ ውስጥም የተቃዋሚው ወገን በሰፊው መሳተፍ ይኖርበታል»
አነ አልሜሊንግ/አርያም ተክሌ
ማንተጋፍቶት ስለሺ