የታሊባን ምክትል አዛዥ መያዝ
ማክሰኞ፣ የካቲት 9 2002ማስታወቂያ
አንድ የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣን የአፋጊስታን ታሊባኖች መሪ የሙላህ ኦማር ምክትል አብዱል ጋህኒ ባራዳር በደቡብ ፓኪስታንዋ የካራቺ ከተማ መያዛቸውን ዛሬ አረጋግጠዋል ። የታሊባኑ ምክትል አዛዥ ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ባለስልጣኑ አስታውቀዋል ። የታሊባን ቃል አቀባይ ግን ባራዳር አፍጋኒስታን ውስጥ ናቸው ሲል አስተባብሏል ። የዶይቼቬለዋ Sabine Matthay የዘገበችውን ሂሩት መለሰ አጠናቅራዋለች ።
ዛቢነ ማታይ/ ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ