1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የትራምፕ እና ኪም ውይይት ያለ ውጤት መቋጨቱ

ሐሙስ፣ የካቲት 21 2011

ቬየትናም ሃኖይ ከተማ ትናንት ለሁለተኛ ጊዜ ለመነጋገር የተገናኙት የዩናይትድ ስቴትስ እና ሰሜን ኮርያ መሪዎች ስብሰባ ያለ ውጤት ድንገት መቋረጡ እየተነገረ ነው። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ እና ፕሬዝደንት ኪም ዮንግ ዑን የአሜሪካን ማዕቀብ አስመልክቶ ያላቸውን አቋም ማለዘብ ባለመቻላቸው የኒኩሊየር ስጋትን ለማስቆም የታለመለት ስብሰባቸው ተቋርጧል።

https://p.dw.com/p/3EHJJ
Vietnam l Hanoi, US-Präsident Donald Trump trifft den nordkoreanischen Staatschef Kim Jong Un - Gipfel ohne Einigung beendet
ምስል picture alliance/dpa/E. Vucci

በቬየትናሟ ሃኖይ ከተማ ትናንት ለሁለተኛ ጊዜ ለመነጋገር የተገናኙት የዩናይትድ ስቴትስ እና ሰሜን ኮርያ መሪዎች ስብሰባ ያለ ውጤት ድንገት መቋረጡ እየተነገረ ነው። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ እና ፕሬዝደንት ኪም ዮንግ ዑን የአሜሪካን ማዕቀብ አስመልክቶ ያላቸውን አቋም ማለዘብ ባለመቻላቸው የኒኩሊየር ስጋትን ለማስቆም የታለመለት ስብሰባቸው ተቋርጧል። ትራምፕ ሰሜን ኮርያ የኒኩሊየር መሣሪያዋን ለማጥፋት ቁጠኝነት ሳታሳይ በዋሽንግተን የተጣለባት ማዕቀብ እንዲነሳ ግፊት ማድረጓን ለንግግራቸው ድንገት መቋረጥ በምክንያትነት ማቅረባቸውንም አክሎ አመልክቷል። የውይይታቸውን ድንገት መቋረጥ አስመልክተው መግለጫ የሰጡት ትራምፕ ያም ቢሆን ሰሜን ኮርያ የሮኬት ፍተሻ ማድረጓን ታቆማለች የሚል ቃል ከኪም ጆን ዑን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል።
«ይህም ቢሆን ዋናው ነገር ሊቀመንበር ኪም ትናንት ማታ የሮኬቶች እና ኒኩሊየር ሙከራ እንደማያደርጉ ቃል ገብተዋል። ስለዚህ እኔም አምናቸዋለሁ እናም ቃላቸውን ተቀብያለሁ። ይህም እውነት ነው ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ሆኖም ግን በመካከሉም እንነጋገራለን። ምክንያቱም ይህ የሚቀጥል ሂደት ነው። ነገር ግን ዛሬ መፈራረሙ ተገቢ ነው ብለን አላሰብንም። »
እንዲያም ሆኖ በሁለቱ ወገኖች መካከል የተደረገው ንግግር ድንገት መቋረጡ እጅግም እንዳልገረማቸው አስተያየት የሚሰጡ ጥቂት አይደሉም። 

 

ሸዋዬ ለገሰ

አዜብ ታደሰ