1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኒደርዛክሰን ምርጫ

ማክሰኞ፣ ጥር 14 2005

CDU ከተሸነፈባቸው ግዛቶች ውስጥ ለረዥም ጊዜ ሲያስተዳድር የቆየው ደቡባዊው ባድን ቩርተንበርግና ፣ የብዙ ህዝብ መኖሪያ የሆነው ራድዮ የኖርድራይን ቬስትፋለን ፌደራል ክፍለ ግዛቶች ይገኙበታል ። በእነዚህ ግዛቶችና

https://p.dw.com/p/17Pd1
SPD-Spitzenkandidat Stephan Weil feiert am 20.01.2013 auf der Wahlparty der SPD in Hannover (Niedersachsen) am Abend der Landtagswahl 2013 in Niedersachsen. Foto: Rolf Vennenbernd/dpa +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

 በኒደርዛክሰን የገጠመው ሽንፈት ለሜርክል በመጪው አጠቃላይ ምርጫ የማስጠንቀቂያ ምልክቶች መሆናቸውን ተንታኞች ያስረዳሉ ።

ባለፈው እሁድ በጀርመኑ የኒደርዛክሰን ፌደራዊ ክፍለ ሃገር ምክር ቤት የተካሄደው ምርጫ ውጤት እዚህ ጀርመን ማነጋገሩ ቀጥሏል ። ግዛቲቱን ላለፉት 10 አመታት ያስተዳደረው የክርስቲያን ዲሞክራት ህብረት ፓርቲ በዚህ ምርጫ መሸነፉ በመጪው መስከረም በሚካሄደው የጀርመን አጠቃላይ ምርጫ ውጤት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ሊያሳድር ይችላል የሚል ግምት አሳድሯል ። ሰሜን ምዕራብ ጀርመን የሚገኘው የኒደርዛክሰን ፌደራዊ ክፍለ ሃገር ከ16ቱ የጀርመን ፌደራል ክፍለ ግዛቶች በስፋት ሁለተኛው ነው ። በህዝብ ብዛት ደግሞ አራተኛውን ስፍራ ይይዛል ። ዋና ከተማይቱ ሃኖቨር ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂ ምርቶች የሚተዋወቁባቸው ዓለም አቀፍ ዓውደ ርዕዮችን እንዲሁም ባህላዊ ና የታሪካዊ ትርኢቶች በማስተናገድ የምትታወቅ ከተማ ናት ። ቮክስቫገንና አውዲን የሚያመርተው ትልቁ የአውቶሞቢል ኢንዱስትሪ ቮክስዋገን ፤ የሚገኝበት በዚሁ ግዛት ሥር ያለው ቮልፍስቡርግ የተባለው ከተማም የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል ነው ። ሌሎችም የንግድ እንቅስቃሴዎች የሚያመዝንባቸው ከተሞች የሚገኙባትን የኒደርዛክሰን ፌደራዊ ክፍለ ግዛት ወግ አጥባቂው የክርስቲያን ዲሞክራት ህብረት ፓርቲ በጀርመንኛው ምህፃር CDU ና ግራ ዘመሙ የሶሻል ዲሞክራቶች ፓርቲ SPD እየተፈራረቁ መርተዋል ።

HANOVER, GERMANY - JANUARY 20: David McAllister (R), incumbent gubernatorial candidate of the German Christian Democrats (CDU), and Social Democrats (SPD) candidate Stephan Weil greet one another following a television news interview after initial poll results gave the CDU and SPD an even number opf seats with their respective coalition partners following elections in Lower Saxony on January 20, 2013 in Hanover, Germany. Many see the Lower Saxony election as a bellwether for national elections scheduled for later this year. (Photo by Sean Gallup/Getty Images)
ምስል Getty Images

SPD ከ1946 እስከ 1955 ከዚያም 1959 እስከ 1976 በኋላም ከ1990 እስከ 2003 ድረስ ፣ CDU ደግሞ እ.ጎ.አ ከ1955 እስከ 1959 እንዲሁም ከ1976 እስከ 1990 ከዚያም ከ2003 እስከ 2013 ድረስ ኒደርዛክሰንን አስተዳድረዋልል ። ባለፈው እሁድ በተካሄደው ምርጫም ግዛቲቱን ለ 10 ተከታታይ አመታት የመራው CDU ባልተጠበቀ ሁኔታ ሲሸነፍ SPD ና አረንጓዴዎቹ በምክርቤት አብላጫ መቀመጫ በማግኘታቸው በግዛቲቱ የበላይነቱን ይዘዋል  ። በአሁኑ ምርጫ CDU 14 የምክር ቤት መቀመጫዎን ሲያጣ SPD ደግሞ 1 ተጨማሪ መቀመጫ አሸንፏል ። አረንጓዴዎቹ ደግሞ እስከዛሬ ከፍተኛ የተባለ 14 በመቶ የመራጭ ድምፅ በማሸነፍ ካለፈው ምርጫ በ6 በመቶ ከፍ ያለ ውጤት አስመዝግበዋል ። ወሳኝ የተባለው የዚህ ምርጫው ውጤት መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ለሚመሩት CDU ታላቅ ሽንፈት ከመሆኑም በላይ በመጪው አጠቃላይ ምርጫ ላይም ከፍተኛ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ተገምቷል ። እዚህ ጀርመን ፍራንክፈርት ነዋሪ የሆኑት የፖለቲካ ተንታኝ ዶክተር ለማ ይፍራሸዋ የከትናንት በስተያው የኒደርዛክሰን ምክር ቤት ምርጫ ውጤት እንዲህ ገምግመውታል ።

Berlin/ Die Spitzenkandidaten der Gruenen fuer die Landtagswahl in Niedersachsen, Stefan Wenzel (v.l.) und Anja Piel, und der Vorsitzende der Bundestagsfraktion von Buendnis 90/Die Gruenen, Juergen Trittin, am Montag (21.01.13) in Berlin auf einer Pressekonferenz zur Landtagswahl in Niedersachsen. Am Sonntag (20.01.13) wurde in Niedersachsen ein neuer Landtag gewaehlt. (zu dapd-Text)
ምስል dapd

የኒደርዛክሰኑ ምርጫ ውጤት ለ CDU ማስጠንቀቂያ ተድርጎ ነው የተወሰደው ። ገዥው CDU ባለፉት 2 አመታት ውስጥ በ 5 ፌደራል ክፍለ ግዛቶች በSPD ተሸንፏል ። CDU ከተሸነፈባቸው ግዛቶች ውስጥ  ለረዥም ጊዜ ሲያስተዳድር የቆየው ደቡባዊው ባድን ቩርተንበርግና ፣ የብዙ ህዝብ መኖሪያ የሆነው ራድዮ ጣቢያችን የሚገኝበት የኖርድራይን ቬስትፋለን ፌደራል ክፍለ ግዛቶች ይገኙበታል ። በእነዚህና ከትናንት በስተያ በኒደርዛክሰን የገጠመው ሽንፈት ለሜርክል በመጪው አጠቃላይ ምርጫ የማስጠንቀቂያ ምልክቶች መሆናቸውን ተንታኞች ያስረዳሉ ። ከዚህ ሌላ ውጤቱ በሜርክል አገዛዝ ላይ ችግር ሊፈጥር እንደሚችልም ይነገራል ። ዶክተር ለማ ምክንያቱን ያብራራሉ

በሌላ በኩል  SPDም ቢሆን በግዛቱ ያገኘው 1 ተጨማሪ መቀመጫ በመሆኑ ያን ያህል የሚያዝናናው እንዳልሆነ ነው ዶክተር ለማ ያስረዱት ። በግዛቲቱ ያለ ጥርጥር አሸናፊዎች አረንጓዴዎች ብቻ መሆናቸው ነው ተደጋግሞ ይነገራል ። ኒደርዛክሰን በ1970ዎቹ የግዛቱቱ መንግሥት ይደግፈው የነበረውን የኒክልየር ዝቃጭ ማስወገጃ ይቃወሙ የነበሩ የጀርመን የአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች አንዷ የእንቅስቃሴ ማዕከል ነበረች ። ይህንም መሰሉ ተቃውሞም እጎገ በ1980 የአርንጓዴዎቹ ፓርቲ ምስረታ እውን እንዲሆን አድርጓል ። 

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ