1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአሜሪካዋ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር በአፍሪቃ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 25 2004

ክሊንተን ኢትዮጵያን ግን አይጎበኙም።እርግጥ ነዉ የሚሰናበቱት፥ የሚያመሰግኑት የኢትዮጵያ መሪም አዲስ አበበ መኖራቸዉ አጠራጣሪ ነዉ።ክሊንተን በቅርቡ የተመረጡትን የአፍሪቃ ኮሚሽን ፕሬዝዳት ድላሚኒ ዙማን ችላ ማለታቸዉን ዶክተር ሲለርስ «አስገራሚ» ብለዉታል

https://p.dw.com/p/15hql
Secretary of State Hillary Rodham Clinton makes a statement regarding the death of Osama bin Laden, Monday, May 2, 2011, at the State Department in Washington. (Foto:Jacquelyn Martin/AP/dapd)
ክሊንተንምስል AP



የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ሒላሪ ክሊንተን በተለያዩ የአፍሪቃ ሐገራት የሚያደርጉትን ጉብኝት ትናንት ማታ ከሴኔጋል ጀምረዋል።ክሊንተን አስራ-አንድ ቀናት በሚፈጅ ጉዟቸዉ ሰባት የአፍሪቃ ሐገራትን ይጎበኛሉ።የጉብኝቱ አላማ ከሐገር ሐገር ቢለያይም ጥቅል ተልዕኮዉ ግን፥ የአሜሪካ ባለሥልጣናት እንዳሉት፥ አፍሪቃዉያን ሠላምና መረጋጋት ለማስፈንና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት የሚያደርጉትን ጥረት ለማበረታት ነዉ።ርዕሠ-መንበሩ ፕሪቶሪያ ደቡብ አፍሪቃ የሚገኘዉ የፀጥታ ጥናት ተቋም ሐላፊ ዶክተር ጃኪ ሲለርስ እንደሚሉት ደግሞ ጉብኙ የአፍሪቃ ተፈላጊነት እያደገ መምጣቱንም አመልካች ነዉ።ነጋሽ መሐመድ አጭር ዘገባ አለዉ።


ጉብኝቱ በሁለት ነገር ከወትሮዉ ይለያል።ብዙ ሐገሮችን በመጎብኘት ከአሜሪካ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ሁሉ ወይዘሮ ሒላሪ ክሊንተንን አንደኛ ያደርጋቸዋል።በሥፖርተኞች ቋንቋ ሪከርድ ይሰብራሉ።-አንድ።

በሚቀጥለዉ ዓመት መግቢያ ጡረታ ለመዉጣት ሥላሰቡ በዘመነ-ሥልጣናቸዉ የተባበሩዋቸዉን የአፍሪቃ መሪዎች ያመሰግናሉ።ይሰናበታሉም።ሁለት።ግን የፖለቲካ ተንታኝ ዶክተር ጃኪ ሲለርስ እንደሚሉት ጉብኝቱ ከዚሕም በላይ ነዉ።
                   
«እንደሚመስለኝ ይሕ ከስንብት በጣም የበለጠ ነዉ።ባለፉት አንድና ሁለት ዓመታት አፍሪቃ በዓለም ያላት ተቀባይነት እየተለወጠ ነዉ።በዩናይትድ ስቴትስ ጭምር።ቀደም ሲል አፍሪቃ የምትታየዉ እርዳታ የማይበቃት ጉድ፥ በሙስና የተዋጠችና የአሸባሪዎች መናኸሪያ ተደርጋ ነበር።አሁን ግን አፍሪቃ በዓለም አቀፍ ያላት ተፈላጊነት እየጨመረ ነዉ።ለመወረቻነት፥ ለጥሬ ዕቃ ምንጭነት ትፈለጋለች።ሐምሳ አራቱ ሐገራት በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ ያላቸዉ ተፈላጊነት እየበረታ ነዉ።»

ይሕ የአፍሪቃ ለዉጥ-ዶክተር ሲለርስ እንደሚሉት የዩናይትድ ስቴትስን ትኩረትን ስቧል። ሥለ አፍሪቃ ያላትን መርሕና አመለካከትም ለዉጧልም።አሜሪካኖችን የሳበዉ የአፍሪቃ ለዉጥ መሠረት ግን በርግጥ አፍሪቃዉያን እራሳቸዉን ያመጡት ነዉ? ወይስ ቻይና እና ሕንድን የመሳሰሉት አዳዲሶቹ ሐብታሞች አፍሪቃ መግባታቸዉ?
                
«በጣም ጥሩ ጥያቄ ነዉ።ምክንያቱም ዩናይትድ ስቴትስ ከቻይና ጋር የገጠመችዉ ፉክክር የአሜሪካንን የዉጪ መርሕ ማረቁ ምንም ጥርጥር የለዉም።የአፍሪቃን ገበያ ለማግኘት በዩናይትድ ስቴትስና በቻይና መካካል የሚደረገዉ ዉድድርም እየተጠናከረ ነዉ።ግን ይሕ ብቻ አይደለም አፍሪቃ ለአሜሪካ ሸቀጥ ጥሩ ቅምጥ ገበያነቷም ግንዛቤ አግኝቷል።»

ወይዘሮ ክሊንተን የደቡብ ሱዳኑን ፕሬዝዳት ሳልቫ ኪርን ሲያነጋግሩ ሁለቱ ሱዳኖች በሚያደርጉት ድርድር «የታየዉን ቀና ለዉጥ-ያበረታታሉ» ይላል-የአሜሪካ ባለሥልጣናት መግለጫ።የሱዳኖች ድርድር ግን ከአዲስ አበበባ ወደ ባሕርዳር ከመዛወሩ ሌላ በነበረበት እየረገጠ ነዉ።

እና የሚበረታታዉ ዉጤት በርግጥ ግራ ነዉ።የትልቂቱ ሐገር ትልቅ ዲፕሎማት ጁባን መጎብኘት ግን ለአዲሲቱ ደሐ-ሐገር ትልቅ ትርጉም አለዉ።የትልቂቱ ሐገር ትልቅ ጥቅምም ከጁባና ካርቱም በላይ ድፍን ሳሔልን ያጠቃልላል።
                
«የሱዳኑን ጦርነት ለማስቆምና በዉጤቱም ሱዳንን ሰሜንና ደቡብ ሱዳን በመክፈሉ ሒደት ዩናይትድ ስቴትስ ትልቅ ሚና ተጫዉታለች።ሥለዚሕ እነሱ አሜሪካኖች በጣም ጠቃሚ ናቸዉ።ዩናይትድ ስቴትስ ሱዳን ዉስጥ ተፅኖ አላት።ከዳካር እስከ ሱዳን በሚደርሰዉ የሳሔል አካባቢ በቅርብ መከታተል ትፈልጋለች።በሳሔል አካባቢ ያለዉ አለመረጋጋት ዩናይትድ ስቴትስን ያሰጋል።»

በሳሔል አካባቢ የተበረካተዉ የአሸባሪዎች፥ የሽፍቶችና የአደንዛዥ ዕፅ ነጋዴዎች ዝዉዉር ሲለርስ እንደሚሉት አሜሪካኖችን ሲበዛ ያሳስባል።ክሊንተን በናይሮቢ ቆይታቸዉ ከኬንያ ሌላ የሶማሊያዉን ፕሬዝዳት ሼኽ ሸሪፍንም ያነጋግራሉ።
                   
«ኬንያና ኢትዮጵያ ባካባቢዉ ለዩናይትድ ስቴትስ ዋነኛ ተባባሪዎች ናቸዉ።እርግጥ ደቡብ ሱዳንም አለች።ግን ደሐ፥ አቅመ ትንሽና አዲስ ሐገር ናት።እና አሜሪካ በሶማሊያ ሠላም ለማስፈን በሚደረገዉ አፍሪቃ መራሽ ጥረት መካፈል፥ መደገፍም ትሻለች።በተለይ ኬንያ፥ አሚሶምና ኢትዮጵያ የሚደርጉትን ጥረት።»
 
ክሊንተን ኢትዮጵያን ግን አይጎበኙም።እርግጥ ነዉ የሚሰናበቱት፥ የሚያመሰግኑት የኢትዮጵያ መሪም አዲስ አበበ መኖራቸዉ አጠራጣሪ ነዉ።ክሊንተን የአፍሪቃ ሕብረት መሪዎችን በተለይም በቅርቡ የተመረጡትን የሕብረቱን ኮሚሽን ፕሬዝዳት ድላሚኒ ዙማን ችላ ማለታቸዉን ግን ዶክተር ሲለርስ «አስገራሚ» ብለዉታል።ብቻ ዳካር፥ ጁባ፥ናይሮቢ፥ ሉሉንግዌ፥ ፕሪቶሪያ፥ ካምፓላን ጎብኝተዉ፥ አክራ ላይ ለቅሶ ደርሰዉ ወደ ሐገራቸዉ ይመለሳሉ።

ነጋሽ መሐመድ

In this image released by the Kenyan Presidential Press Service President, President Mwai Kibaki addresses the nation during a live televised new year address to the nation at State House, Nairobi, Tuesday, Jan. 1, 2008. Kenyans ventured out in search of food on Tuesday after four days of violence killed more than 200 people and President Mwai Kibaki came under increasing pressure for what protesters called his sham re-election.The post election violence, which flared from the shantytowns of Nairobi to resort towns on the sweltering coast, has left 202 people dead since Saturday, according to accounts from police, morgues and witnesses Tuesday was calmer, although skirmishes were still reported in Nairobi's slums, which are home to tens of thousands of opposition supporters. Much of the capital has been a ghost town as residents hunkered down in their homes. (AP Photo- Presidential Press Services-HO)
ኪባኪምስል AP/Presidential Press Services
Senegalese opposition presidential candidate Macky Sall speaks at a celebratory news conference in the capital Dakar March 25, 2012. Senegal's long-serving leader Abdoulaye Wade admitted defeat in the presidential election, congratulating his rival Sall, a move seen as bolstering the West African state's democratic credentials in a region fraught with political chaos. REUTERS/Joe Penney (SENEGAL - Tags: POLITICS ELECTIONS PROFILE)
ሳልምስል REUTERS

ተክሌ የኋላ


 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ