1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአረብ አብዮት የገጠመዉ እንቅፋት

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 21 2005

የግብፅ ጦር ሐይል በሐገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሕዝብ የተመረጡትን ፕሬዝዳትን ከሥልጣን ማስወገዱ፥ መፈንቅለ መንግሥቱን የሚቃወሙ ወገኖችን መግደል፥ ማሰሩ ብዙ ሲያነጋግር፥ሕዝባዊ አብዮት ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀጣጠለባት አምባገናናዊዉን ሥርዓት በምርጫ የተኩት የቱኒዚያ ፖለቲከኞች እርስ በርስ እየተወዛገቡባት ነዉ

https://p.dw.com/p/19Xb9
Abgeordnete der Verfassunggebenden Versammlung in Tunis boykottieren das Gremium und fordern den Sturz der Regierung am 13.8.2013 Ich habe die Fotos selbst gemacht und bin damit einverstanden, dass Sie unter Nennung meines Namens auf den Seiten der Deutschen Welle veröffentlicht werden. DW/A. Allmeling
ቱኒዚያ ሠልፍምስል DW/A. Allmeling

የግብፅ ጦር ሐይል በሐገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሕዝብ የተመረጡትን ፕሬዝዳትን ከሥልጣን ማስወገዱ፥ መፈንቅለ መንግሥቱን የሚቃወሙ ወገኖችን መግደል፥ ማሰሩ ብዙ ሲያነጋግር፥ በሕዝባዊ አመፅ ከስልጣን የተወገዱትና ሰዎች’ በማስገደል የተከሰሱት የቀድሞዉ ፕሬዝዳት ሆስኒ ሙባረክ ከወሕኒ ቤት ተለቀዋል።ከሁለት ዓመት በፊት የአረቡን ዓለም ያነቃነቀዉ ሕዝባዊ አብዮት ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀጣጠለባት አምባገናናዊዉን ሥርዓት በምርጫ የተኩት የቱኒዚያ ፖለቲከኞች እርስ በርስ እየተወዛገቡባት ነዉ።የሊቢያ ሕዝባዊ አብዮት በቅፅበት ወደ ጦርነት ሲለወጥ፥ የሶሪያዉ የእርስ በርስ ጦርነት ምዕራባዉያንን በቀጥታ ጣልቃ ለማስገባት የመጨረሻ ደረጃ ደርሷል።መፈንቅለ መንግሥቱ፥ ዉዝግብና ጦርነቱ ብዙ ተስፋ የተደረገበት የአረብ ሕዝባዊ አብዮት ፍፃሜ ይሆን? የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ ይጠይቃል።መልስ ሰጪም አነጋግሯል።

ገበያዉ ንጉሴ

ነጋሽ መሀመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ