1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአረና እና ታድ መግለጫ

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 10 2011

ፓርቲው ከትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር እንቅስቃሴ ጋር በጋራ በሰጠው መግለጫ በክልሉ ሰላማዊ የፓለቲካ እንቅስቃሴ ማድረግ አስቸጋሪ እየሆነብን ነው ብለዋል፡፡ለዶቼቬለ DW ስለጉዳዩ የጠየቃቸው ወጣቶቹ የታሰሩበት የኪውሀ አካባቢ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ አልነበሩም፤ ፖሊስን ሲተነኩሱ በቁጥጥር ስር ውለዋል ሲል ተናግሯል።

https://p.dw.com/p/3H2er
Äthiopien PK Abraha Desta und Mekonnen Zelelew
ምስል DW/Million Haileselassie

የአረና እና የታድ መግለጫ

 

በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ የነበሩ አባላቶቼ ደጋፊዎቼ ታሰሩ ሲል ዓረና ትግራይ ለሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ ገለፀ፡፡ ፓርቲው ከትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር እንቅስቃሴ ጋር በጋራ በሰጠው መግለጫ በክልሉ ሰላማዊ የፓለቲካ እንቅስቃሴ ማድረግ አስቸጋሪ እየሆነብን ነው ብለዋል፡፡ለዶቼቬለ DW ስለጉዳዩ የጠየቃቸው ወጣቶቹ የታሰሩበት የኪውሀ አካባቢ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ አልነበሩም፤ ፖሊስን ሲተነኩሱ በቁጥጥር ስር ውለዋል ሲል ተናግሯል። የመቀሌው ዘጋቢያችን ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ ዝርዝር ዘገባ አለው።  
መቀሌ ኃይለ ሥላሴ
ኂሩት መለሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ