1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአትሌት ታምሩ ደምሴ ተቃውሞ

ማክሰኞ፣ መስከረም 3 2009

በብራዚል እየተካሄደ በሚገኘው 15ኛው የፓራ ኦሎምፒክ ውድድር ላይ ባለፈው እሁድ በ1500 ሜትር ሩጫ ውድድር የብር ሜዳሊያ ለሀገሩ ያስገኘው ታምሩ ደምሴ የተቃውሞ ምልክት ማሳየቱ አሁንም እያነጋገረ ይገኛል፡፡

https://p.dw.com/p/1K1Wc
Brasilien Paralympics Rio 2016 Tamiru Demisse
ምስል Getty Images/M. Stockman

የተቃውሞ ምልክቱን በሜዳሊያ አሰጣጥ ስነ ስርዓቱ ላይም የደገመው ታምሩ ድርጊቱን ያደረገው የኢትዮጵያ መንግስት እየወሰደ ያለውን የኃይል እርምጃ ለዓለም ህዝብ ለማሳየት እንደሆነ ይናገራል፡፡ ታምሩ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ እንደማይፈልግ እና ከዓለምአቀፉ ፓራኦሎምፒክ ኮሚቴ እገዳ ሊጣልበት እንደሆነ መስማቱን ለዶየቸ ቨለ ገልጿል፡፡ በእንግድነት ብቅ ያለው ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ከሌሊሳ ፈይሳ በኋላ በኦሎምፒክ መንደር በድጋሚ ተቃውሞውን ያሳየውን አትሌት ታምሩን አነጋግሮታል፡፡አትሌቱ በውድድሮች ላይ ስለነበረው ተሳትፎ በመግለጽ ይጀምራል።

ተስፋለም ወልደየስ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ