የአቶም ሳይንቲስቱ ዶ/ር ጌድዮን ጌታሁን
ማክሰኞ፣ የካቲት 12 2005
ቀጣዩ አውሮፓና እዚህ ጀርመን ከተማሩና ለበርካታ አመታት ከሰሩ አንድ የአቶም ሳይንቲስት ጋር ያስተዋውቀናል ።
በምዕራብ ጀርመኑ የራይንላንድፋልስ ፌደራዊ ክፍለ ሃገር ዋና ከተማ ማይንዝ በሚገኘው ዪሐንስ ጉተንበርግ ዩኒቨርስቲ የአቶም ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ ናቸው ። ካለፈው አመት ጀምሮ ደግሞ ዳርምሽታት በተባለው ከተማ ውስጥ በሚካሄድ የምርምር ሥራ ተካፋይ ናቸው የዛሬው እንግዳችን ዶክተር ጌድዮን ጌታሁን ።
የራድዮ አናሊቲካል ኬሚስትሬ ምሁር ዶክተር ጌድዮን የሙያቸውን ምንነትና ጥቅሙን በቅድሚያ ይነግሩናል ።
ዶክተር ጌድዮን ጀርመን ለትምህርት የመጡት በ1966 ሲሆን መጀመሪያ በባየርንዋ ሙርናው ከተማ የቋንቋ ትምሕርት ከተከታተሉ በኋላ በሽቱትጋርት የኬምስትሪ ትምሕርት ከተከታተሉ በኋላ እዚያው ሽቱትጋርት ውስጥ ሥራ ያዙ ። ከዚያም ወደ ዳርምሽታት በመሄድ የኬሚካል ኢንጅነሪንግ ትምሕርት ተከታትለው በኋላ በዚያ ከተማ ለረዥም ጊዜ በፋርማሲቲካል ኢንዱስትሪ ሰሩ ። ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ደግሞ ሌላ ትምህርት የመከታተል እድል አገኙ ። ዶክተር ጌታሁን የአቶም ሳይንስ ለማጥናት ሲወስኑ ምክንያት ነበራቸው ።
ከ1995 አም አንስቶ በማይንዝ የኒዩክልየር ሳይንስ ተቋም ሥራ አግኝተው አሁን እዚያው በመሥራት ላያይ ናቸው ። ዶክተር ጌታሁን ከዚህ ሌላ ለከተማዋ የ SPD ፓርቲ በሞያቸው እያገለገሉ ነው
ምንም እንኳን ዶክተር ጌድዮን የሚሰሩት ጀርመን ቢሆንም ሃገራቸውንና ህዝባቸውን አልረሱም ለረዥም ጊዜ በሊቀመንበርነት በሊቀመንበርነት በመሩት ማህበር አማካይነትና በግላቸው የኢትዮጵያን የሳይንስ ትምሕርትና ተማሪዎች ይረዳሉ ።
ዶክተር ጌታሁን እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሃገራት የኬምስትሪ ትምሕርትን ለማስፋፋፋት ወከናወን ያለባቸውን ተግባራት ጠቁመዋል ።
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሰ