1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተመድ ዋና ጸሀፊ አስተያየት

ማክሰኞ፣ የካቲት 20 2010

ድርጅቱ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥልጣን መልቀቅ ጥያቄ ላይ አስተያየት መስጠቱ እንዴት ይታያል ሲል ዶቼቬለ የጠየቃቸው አንድ የፖለቲካ ተንታኝ ድርጅቱ አስተያየት የሰጠው የኢትዮጵያ ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ነው ሲሉ በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ፅህፈት ቤት ቃል አቀባይ ደግሞ ድርጅቱ አስተያየት መስጠቱ አዲስ ነገር አይደለም ብለዋል።

https://p.dw.com/p/2tQPT
UN-Generalsekretär Antonio Guterre
ምስል imago/Kyodo News

የአቶ ኃይለማርያም ስልጣን የመልቀቅ ጥያቄ እና የተመድ አስተያየት

 

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሥልጣን ለመልቀቅ ያሳለፉትን ውሳኔ በበጎ መቀበሉን አስታወቀ። የድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶንዮ ጉተሬሽ የአቶ ኃይለ ማርያም ውሳኔ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እድል የሚሰጥ እርምጃ ነው ብለዋል። ድርጅቱ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥልጣን መልቀቅ ጥያቄ ላይ አስተያየት መስጠቱ እንዴት ይታያል ሲል ዶቼቬለ የጠየቃቸው አንድ የፖለቲካ ተንታኝ ድርጅቱ አስተያየት የሰጠው የኢትዮጵያ ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ነው ሲሉ በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ፅህፈት ቤት ቃል አቀባይ ደግሞ ድርጅቱ አስተያየት መስጠቱ አዲስ ነገር አይደለም ብለዋል። መክብብ ሸዋ ከዋሽንግተን ዲሲ ዝርዝር ዘገባ አለው። 

መክብብ ሸዋ

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ