የአቶ አሥራት ጣሴ ይግባኝ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 23 2006ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ፌደራል ከፍተና ፍርድ ቤት 11ኛ ይግባኝ ሰሚ ልዩ ችሎት ለአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአመራር አባል ለአቶ አስራት ጣሴ ይግባኝ ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ ። አቶ አስራት ዛሬ በጠበቃቸው በኩል ለልዩ ችሎቱ ባቀረቡት ይግባኝ በአንድ የግል መፅሄት ላይ ፍርድ ቤቱን በመድፈርና በመተቸት ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የተጣለባቸው የ2 ዓመት ገደብ እንዲነሳላቸው ጠይቀው ነበር ። ሆኖም ችሎቱ ይግባኙ ረዝሟል ሲል ፍሬ ነገሩ ላይ አትኩሮ አጠር ብሎ እንዲቀርብለት በማዘዝ ለሚያዚያ አንድ ቀን 2006 ዓም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ