የአቶ ግርማ አስተያየት
ሐሙስ፣ የካቲት 1 2010ማስታወቂያ
ታራሚ እና ተጠርጣሪ እስረኞችን ለመፍታት መወሰኑን ያሳወቀው መንግሥት እርምጃው በጎ ፋይዳ እንዲኖረው የፖለቲካ ምህዳሩንም እንዲያሰፋ ተጠየቀ ። ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌን ጨምሮ 746 ታራሚዎች እና ተጠርጣሪዎች እንዲለቀቁ ተወስኗል መባሉ እንዳስደሰታቸው ለዶቼቬለ የተናገሩት የቀድሞ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ግርማ ሰይፉ የመደራጀት የሃሳብን በነጻ የመግለጽና የመሳሰሉትን መብቶች በማክበር የፖለቲካ ምህዳሩን እንዲያሰፋ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ታራሚዎችን እና ተጠርጣሪዎችን ለመፍታት ስለደረሰበት ውሳኔ ፋይዳ እና ከአሁን በኋላ ከመንግሥት ስለሚጠበቀው አቶ ግርማ የሰጡትን አስተያየት ያካተተውን ቃለ ምልልስ የድምጽ ማዕቀፉን በመጫን ያዳምጡ
ኂሩት መለሰ
ተስፋለም ወልደየስ
አዜብ ታደሰ