1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአንዳርጋቸዉ ፅጌ መታሠር

ረቡዕ፣ ሰኔ 25 2006

ግንቦት ሰባት እንደሚለዉ የብሪታንያ ዜግነት ያላቸዉ አቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌ ባለፈዉ ሳምንት ሰኞ የመን አዉሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በፀጥታ አስከባሪዎች ከተያዙ በኋላ ያሉበት ሥፍራና ሁኔታ አይታወቅም

https://p.dw.com/p/1CUdv
የአንዳርጋቸዉ ፅጌ መታሠር
ምስል DW/S. Alsoofi

በሥደት የሚገኘዉ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚ ፓርቲ ግንቦት ሰባት የመን ዉስጥ የታሠሩትን ዋና ፀሐፊዉን አቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌን ለማስፈታት የተለያዩ ዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ዘመቻዎች መጀመሩን አስታወቀ።አንድ የግንቦት ሠባት ባለሥልጣን እንዳስታወቁት አቶ አንዳርጋቸዉን ለማስለቀቅ የብሪታንያ ዲፕሎማቶችም እየጣሩ ነዉ።በለንደን የየመን ኤምባሲም ጉዳዩን እየተከታተለዉ መሆኑን አስታዉቋል።ግንቦት ሰባት እንደሚለዉ የብሪታንያ ዜግነት ያላቸዉ አቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌ ባለፈዉ ሳምንት ሰኞ የመን አዉሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በፀጥታ አስከባሪዎች ከተያዙ በኋላ ያሉበት ሥፍራና ሁኔታ አይታወቅም።የለንደንዋ ወኪላችን ሐና ደምሴ ዝርዝር ዘገባ ልካልናለች

ሐና ደምሴ

ነጋሽ መሐመድ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ