1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአኺም ሽታይነር እና የሄለን ቢሲምባ አስተያየት

ሰኞ፣ መጋቢት 23 2005

አኺም ሽታይነር - በናይሮቢ የተመድ የተፈጥሮ ጥበቃ መርሀግብር መሥሪያ ቤት ኃላፊ ፣ ዶይቸ ቬለ የተመድ የተፈጥሮ ጥበቃ መሥሪያ ቤት ለሚያከናውነው ሳይንሳዊ ስራ ያሳየውን ትልቅ ትኩረት በዚያ የምንሰራው ሁሉ ትልቅ ትርጉም ሰጥተነዋል። ዶይቸ ቬለ መረጃዎችን ወደ ሕዝቡ ለማድረስ ረድቶናል።

https://p.dw.com/p/18KxL
ምስል picture alliance/dpa

እኛ የተመድ ሰራተኞች ናይሮቢ፡ ሁሉም ስው ፣ ቲምቡክቱ ይሁን በርሊን፡ ዋሽንግተን ወይም ብራዚል የሚኖሩት ሁሉ የምናቀርባቸውን መረጃዎች መልዕክት እኩል በሚረዱልን ሁኔታ ላይ ጥገኞች ነን። ዶይቸ ቬለም ሰዎች ይቀራረቡ ዘንድ ከሚረዱት መገናኛ መድረክ መካከል አንዱ ነው። ስለዚህ ዶይቸ ቬለን ለወደፊቱ ስራው መልካም ዕድል እንመኝለታለን።

------------------------

በዳሬሰላም የሰብዓዊ እና የሕጋዊ መብቶች ተሟጋች ማዕከል ኃላፊ- ሄለን ኪጆ ቢሲምባ

North Mara Gold Mine in Tansania Helen Kijo-Bisimba Direktorin LHRC
ምስል DW/J. Hahn

ዶይቸቬለ ፡ በተለይ የኪስዋሂሊ ቋንቋ፡ ድምፃችን እንዲሰማ ሁሌም ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሮልን ቆይተዋል፤ ምክንያቱም፡ በታንዛንያ ብዙ ሕዝብ በኪስዋሂሊኛ ቋንቋ የሚሠራጨውን ዝግጅት ያዳምጣል። ይህ በጣም በጣም ጠቃሚ ነው። ሰዎች ብዙ መረጃዎችን ከዶይቸ ቬለ የኪስዋሂሊ ቋንቋ ክፍል ዝግጅት እንደሚያገኙ በተደጋጋሚ ሲናገሩ ሰምቻለሁ።