የአዉሮጳ ሕብረት ጦር በማሊ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 24 2005ማስታወቂያ
የአዉሮጳ ሕብረት አባል ሐገራት ማሊ ያዘመቱት አሠልጣኝ ሠራዊት ዛሬ የማሊ ወታደሮችን ማሠልጠን ጀምሯል።ከሁለት መቶ ከሚበልጡት የአዉሮጳ ሕብረት አሠልጣኞች መካካል ሰማንያዉ የጀርመን ወታደሮች ናቸዉ።የሥልጠናዉ አላማ የማሊ ጦር ሰሜናዊ ማሊ የሸመቁ የሙስሊም አክራሪ ደፈጣ ተዋጊዎችን የመዉጋት ብቃቱን ማዳበር ነዉ።የሙስሊም እና የቱአሬግ ደፈጣ ተዋጊዎች የፈረንሳይ ጦር እስከዘመተባቸዉ ጊዜ ድረስ አብዛኛዉ የሰሜናዊ ማሊ ግዛት አብዛኛ ግዛቶች ይቆጣጠሩ ነበር።የአዉሮጳ ሕብረት አሠልጣኖች በአንድ ዓመት ጊዜ ዉስጥ ከሠወስት ሺሕ በላይ የማሊ የጦር መኮንኖችንና ወታደሮች ለማስተማር አቅደዋል።
ይልማ ኃይለሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ