1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮጳ ህብረት ለሶማልያ የሚሰጠው ርዳታ

ማክሰኞ፣ ጥር 18 2002

የአውሮጳ ህብረት የሶማልያ የሽግግር መንግስት የጸጥታ ኃይላትን በዩጋንዳ የሚያሰለጥን አንድ ቡድን ለመላክ ወሰነ።

https://p.dw.com/p/LhEn
የአውሮጳ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ካትሪን አሽተንምስል AP

ሀሳቡን ያካባቢ ሀገሮች፡ የአፍሪቃ ህብረት፡ የተመድ እና ዩኤስ አሜሪካ ደግፈውታል። ይህንኑ ከአባል ሀገሮች የሚውጣጠውን አሰልጣኝ ቡድን ወቅታዊውን የህብረቱን የሚንስትሮች ምክር ቤት ፕሬዚደንትነትን ስልጣን የያዘችው ስጳኝ ትመራለች። ይሁንና፡ የሚሰለጥኑት የጸጥታ ኃይላት አባላት ከሰለጠኑ በኋላ በሽግግር መንግስቱ ውስጥ ማገልገል መቀጠላቸውን የሚያረጋግጥ ዋስትና የለም በሚል አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ለዓለም አቀፍ ውዝግቦች መፍትሄ የሚያፈላልገው ድርጅት ክራይስስ ግሩፕ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ገበያው ንጉሴ/አርያም ተክሌ/ተክሌ የኋላ