የአውሮጳ ህብረት መሪዎች ድህረ ምርጫ ጉባኤ
ሐሙስ፣ ግንቦት 22 2011ማስታወቂያ
የአውሮጳ ሕብረት አባል ሃገራት መሪዎች የሕብረቱ ተቋማት አሠራር ፣ የባለሥልጣናቶቻቸው አመራረጥ እና አሿሿም የምርጫውን ውጤት ያገናዘበ እንዲሆን ተስማምተዋል። የ28 ቱ የሕብረቱ አባል ሃገራት መሪዎች ባለፈው ማክሰኞ ባካሄዱት ጉባኤያቸው ባለፈው ሳምንት መጨረሻ የተካሄደውን የአውሮጳ ህብረት ምክር ቤት ምርጫ ውጤት እና ምንነትን እንዲሁም ያስተላለፈውንም መልዕክት በጥልቀት ገምግመዋል። የብራሰልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሤ ዘገባ አዘጋጅቷል.
ገበያው ንጉሤ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ