1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአየር ንብረት ቀውስና -የዝናም እጦት፣

ረቡዕ፣ ጥቅምት 25 2002

ኢትዮጵያ ውስጥ ዝናም ወቅቱን አልጠብቅ ብሏል። አንዳንዴ ጀምሮ ያቋርጣል፣ መጠኑም ቢሆን እየቀነሰ መምጣቱ እየተስተዋለ ነው።

https://p.dw.com/p/KORd
የአየር ንብረት ቀውስና -የዝናም እጦት፣
ድርቅ የተጠናወተው ቦታ፣ በኢትዮጵያ፣ምስል AP

ውጤቱ ታዲያ በዝናም ብቻ የሚመካን ግብርና፣ መቅኖ የሚያሳጣና ህዝብን ለረሃብ የሚዳርግ ነው የሚሆነው። በመሠረቱ ብዙ ወንዞች በሚፈሱባት አገር ፣ በአንዳንድ ወቅቶች ዝናም በመጥፋቱ ብቻ ህዝብ፣ በምንም ዓይነት ተርቦ ለእልቂት ሊዳረግ ባልተገባው ነበር። በመርኅ ደረጃ፣ አማራጭና ዘላቂ መፍትኄዎችን መሻት የግድ ይላልና! ያም ሆኖ ፣ በአየር ንብረት ላይ ፣ ቀውስ የሚያስከትሉ ሁኔታዎች መከሠታቸው በየአህጉሩ ባለሙያዎችን ማነጋገሩን እንደቀጠለ ነው። በዛሬው ሳይንስና ኅብረተሰብ ቅንብራችን ፣ ከጥቅምት 11-13 ,2002 ዓ,ም ፣ ቦን ውስጥ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አካሂዶት በነበረው፣ በአየር ንብረት ቀውስና በመከላከያ እርምጃዎች ላይ ባጤነ ጉባዔ ተሳትፈው ከነበሩ አንድ ኢትዮጵያዊ የዘርፉ ባለሙያ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ እናሰማለን።

ተክሌ የኋላ/ነጋሽ መሐመድ