የአይነስዉራን የኮንፒዉተር ማሰልጠኛ ተቋም
ሰኞ፣ ኅዳር 15 2001ማስታወቂያ
እ.አ አቆጣተር 1994 አ.ም በአገራችን በወጣዉ ማየት የተሳናቸዉ ሰዎች ቁጥር መዘርዝር እንደሚያሳየዉ ከአንድ ነጥብ ተኩል ሚሊዮን በላይ ማየት የተሳናቸዉ ወገኖች ይገኛሉ። የሚያሳዝነዉ አብዛኛዎቹ ማየት የተሳናቸዉ ግለሰቦች የአይን ብርሃናቸዉን ያጡት በቀላሉ በህክምና ፈዉስ በሚያገኙ እንደትራኮማ ግላኮማ አይነት፣ የአይን በሽታዎች ሲሆን ሌላዉ በግጭቶች እንዲሁም ተፈጥሮዋዊ ሁኔታዎች ነዉ። በአገራችን ብቸኛዉና የመጀመርያዉ የአይነስዉራን የኮንፒዉተር ማሰልጠኛ ድርጅት ከተቋቋመ ስምንት አመት ሲሆነዉ የአለማየት ትርጉምን ያሳጣ መሆኑም ይነገርለታል። በርካታ ወጣቶችንም በመርዳት ላይ ይገኛል። ስለዚህ የኮንፒዉተር ማሰልጠኛ ድርጅት የምንለዉ ይኖረናል አብራችሁን ያድምጡ