1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ«አይ ኤስ» የጭካኔ ተግባር እና የብሪታንያ ውግዘት

ሰኞ፣ መስከረም 26 2007

ራሱን «አይ ኤስ» ወይም እስላማዊ መንግሥት ብሎ የሚጠራው ፅንፈኛ ቡድን ከአንድ ዓመት በፊት በሶርያ አግቶት የነበረውን የ47 ዓመት እንግሊዛዊ አለን ሄኒንግን አንገት ቀልቶ መግደሉን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን በጥብቅ በማውገዝ የብሪታንያ መንግሥት በቡድኑ እና በሀገሪቱ አሉ በሚባሉ የቡድኑ ደጋፊዎች ላይ የማያዳግም ርምጃ እንዲወስዱ ጠይቀዋል።

https://p.dw.com/p/1DR7y
England Fassungslosigkeit Enthauptung IS Geisel Alan Henning
ምስል Getty Images/AFP/O. Scarff

በብሪታንያ የሚኖሩ ሙስሊሞችም የበጎ አድራጎት ስራ ለማከናወን ወደ ሶርያ ተጉዞ የነበረው ሄኒንግን እንዳይገደል ፅንፈኛውን ቡድን ቢማፀኑም፣ ሰሚ ሳያገኙ ነበር የቀረው።ቡድኑ ይህንን አስከፊ የጭካኔ ተግባር የፈፀመው የብሪታንያ የጦር አይሮፕላኖች በ«አይ ኤስ» ወይም በእስላማዊ መንግሥት አንፃር በዩኤስ መሪነት በተጀመረው የጥቃት ዘመቻ መሳተፍ ከጀመረ በኋላ ነበር። ሄኒንግ ቡድኑ ካለፉት ጥቂት ሳምንታት ወዲህ አንገታቸውን ቀልቶ የገደላቸው ሶስተኛው የምዕራቡ ዓለም ተወላጅ ነበሩ።

ድልነሳ ጌታነህ

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ