1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዲሱ የኔቶ ዋና ጸሐፊ ኃላፊነቶችና ተግዳሮቶች

ሰኞ፣ መስከረም 26 2007

ሚስተር የንስ ስቶልቴንበርግ 28 አባል መንግሥታት የሚገኙበትን የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን በእንግሊዝኛ ምህጻሩ ኔቶ አዲስ ዋና ጸሐፊ ሆነው ስራቸውን በይፋ የጀመሩት ባለፈው ረቡዕ ነበር። ስቶልቴንበርግ ግዙፉ የምዕራባዉያን ወታደራዊ ግንባር ከዚህ ቀደም በበላይነት የመሩት አንደርስ ፎኽ ራስሙሰንን ነው የተኩት።

https://p.dw.com/p/1DRDg
Jens Stoltenberg neuer NATO Generalsekretär PK 01.10.2014
ምስል Reuters/Francois Lenoir

አዲሱ የኔቶ መሪ ገና በለጋ እድሜያቸዉ የቬትናትም ጦርነትና አሜሪካንን በመቃወም ወደፖለቲካዉ ዓለም መግባታቸዉ ይነገራል። የኖርዌይ ዜጋ የሆኑት ስቶልቴንበርግ በተለያዩ የስልጣን ርከኖች ላይ በመሆን ሀገራቸዉ ያገለገሉ ሲሆን በተመድ ዉስጥ በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ላይ ሠርተዋል። ፖለቲከኛዉ ከሩሲያዉ መሪ ፕሬዝደንት ቪላድሚር ፑቲን ጋ መልካም ግንኙነት ካላቸዉ ጥቂት የኔቶ አባል ሃገራት መሪዎች አንዱ መሆናቸዉ ይነገራል። በድርጅቱና ሩሲያ ግንኙነት ላይ ለዉጥ ያመጡ ይሆን?

ገበያዉ ንጉሤ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ