1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ኤኮኖሚ

የአዲሱ የካካዎ ተመንን እና ዉጤቱ

ረቡዕ፣ ሰኔ 19 2011

የአፍሪቃ መንግሥታትም ገበሬዎቻቸዉን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለድሕነት  የሚያጋልጠዉን የንግድ ሥርዓት ፍትሐዊ ለማድረግ ብዙም የሚጨነቁ አይመስሉም። በዓለም ከፍተኛዉን የካካኦ ምርት ለገበያ የሚያቀርቡት የጋና እና የኮትዲቯር መንግሥታት ግን በቅርቡ የጋራ የዋጋ ተመን አጥተዋል

https://p.dw.com/p/3L8Gh
Belize NGO Ya'axché
ምስል DW/Katja Döhne

የካካኦ ሽያጭ ተመን

     

የአፍሪቃ ሐገራት ለዓለም ገበያ የሚያቀርቧቸዉ አብዛኞቹ የግብርና ዉጤቶች ከአምራቾቹ ገበሬዎች ይልቅ በአብዛኛዉ የምዕራብ ሐገራት ነጋዴዎችንና ደላሎችን እንደሚጠቅም በተደጋጋሚ ተነግሯል። የአፍሪቃ መንግሥታትም ገበሬዎቻቸዉን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለድሕነት  የሚያጋልጠዉን የንግድ ሥርዓት ፍትሐዊ ለማድረግ ብዙም የሚጨነቁ አይመስሉም። በዓለም ከፍተኛዉን የካካኦ ምርት ለገበያ የሚያቀርቡት የጋና እና የኮትዲቯር መንግሥታት ግን በቅርቡ የጋራ የዋጋ ተመን አጥተዋል። የሁለቱ መንግሥታት ለካካኦ አዲስ ተመን ማዉጣታቸዉ ምናልባት ቡና እና ሌሎች ተመሳሳይ ምርቶችን ለገበያ የሚያቀርቡ የአፍሪቃ መንግሥታት ተመሳሳይ ርምጃ እንዲወስዱ መሠረት ሊሆን ይችላል የሚል አስተያየት አስከትሏል። የዛሬዉ ከኤኮኖሚዉ ዓለም ዝግጅት የአዲሱ የካካዎ ተመንን እና ዉጤቱን ይቃኛል።አንድርያስ ቤከር የዘገበዉን የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለ ሚካኤል አጠናቅሮታል።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ነጋሽ መሐመድ