የአዲስ አመት አከባበር
ማክሰኞ፣ መስከረም 1 2005ማስታወቂያ
ችቦው ተለኩሶ ፣የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ ተብሎ ኢትዮጵያውያን አዲሱን አመት 2005 ን ከተቀበልን አንድ ቀን ልንል ትንሽ ሰዓታት ቀረን ። በሃገር ቤት እንደ ልምድና ወጉ በአሉ ሲከበር በውጭ የሚኖሩት ኢትዮጵያውን ከዚሁ ባልተለየ መንገድ ዘመን መለወጫን ሲያከብሩት ውለዋል ። በአዲስ አበባስ አከባበሩ ምን ይመስል ነበር? የገበያዉስ ሁኔታ? በተለያዩ አገራት የሚገኙ ወኪሎቻችንም የኢትዮጵያዉያንን የአዲስ አመት አከባበር ተመለካክተዉ ዘገባ አድርሰዉናል። በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ይዞታ ስር ያሉ ጥንታዊ ገዳማት በሚገኙበት በእየሩሳሌም ያለዉን የኢትዮጵያዉያን አዲስ አመት አከባበር ቃኝተናል። ቅንብሮቹን ያድምጡ!
አዜብ ታደሰ
ሂሩት መለሰ