1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፋር ሕዝብ ፓርቲ መግለጫ

ማክሰኞ፣ ጥር 1 2004

የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፡ በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ ኤ ፒ ፒ ሰሞኑን ባሰራጨው መግለጫው በርካታ የአፋር ክልል ነዋሪዎች ለእሥር መዳረጋቸውን፡ ያካባቢው አርብቶ አደሮችም የግጦሽ መሬታቸውን እየተነጠቁ ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ መደረጋቸውን አስታወቀ።

https://p.dw.com/p/13hBy


የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፡ በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ ኤ ፒ ፒ ሰሞኑን ባሰራጨው መግለጫው በርካታ የአፋር ክልል ነዋሪዎች ለእሥር መዳረጋቸውን፡ ያካባቢው አርብቶ አደሮችም የግጦሽ መሬታቸውን እየተነጠቁ ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ መደረጋቸውን አስታወቀ። አባላ የሚባለው የክልሉ እሥር ቤትም የክልሉን መንግሥት ይቃወማሉ በተባሉ ያካባቢው ሰላማዊ ሰዎች እና በዘመዶቻቸው የተሞላ መሆኑን መግለጫው አክሎ አመልክቶዋል። የብራስልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሤ የየአፋር ሕዝብ ፓርቲ የውጭ እና የኤኮኖሚ ጉዳይ ኃላፊ፡ ዶክተር ኩንቲ ሙሳን ስለመግለጫው ይዘት፡ በአፋር ክልል ይፈፀማል ስለተባለው እሥርና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ማብራሪያ እንዲሰጡት ጠይቆዋቸዋል።

ገበያዉ ንጉሴ

አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሃመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ