1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ መሪዎች ጉባዔና ኮንጎ፣

ሐሙስ፣ ነሐሴ 3 2004

በምሥራቅ ኮንጎ የተቀሰቀሰውን የትጥቅ አመጽ፤ በገልልተኛ አመጽ ለማረቅ ካምፓላ ላይ የመከሩት የአፍሪቃ መሪዎች፤ ለጊዜው መፍትኄ ሳያስገኙለት እንደገና በአንድ ወር ለመሰብሰብ ተስማምተው ነው ትናንት የተለያዩት። M 23 በመባል በታወቀው አማጺ

https://p.dw.com/p/15nHV
Uganda's President Yoweri Museveni (back C) chairs the International Conference on the Great Lakes Region (ICGLR) at the Commonwealth Resort Hotel Munyonyo in the capital of Kampala August 7, 2012. U.S. Secretary of State Hillary Clinton urged Rwanda and Great Lakes neighbours on Tuesday to stop supporting Congolese rebels as regional leaders met in Uganda to discuss ways to end the insurgency in the eastern Democratic Republic of Congo. REUTERS/Edward Echwalu (UGANDA - Tags: POLITICS)
ምስል Reuters

በምሥራቅ ኮንጎ የተቀሰቀሰውን የትጥቅ አመጽ፤ በገልልተኛ አመጽ ለማረቅ ካምፓላ ላይ የመከሩት የአፍሪቃ መሪዎች፤ ለጊዜው መፍትኄ ሳያስገኙለት እንደገና በአንድ ወር ለመሰብሰብ ተስማምተው ነው ትናንት የተለያዩት። M 23 በመባል በታወቀው አማጺ ኃይልና በኮንጎ መንግሥት ወታደሮች በኩል በተደረገ ውጊያ ሳቢያ፣ ከሞላ ጎደል ግማሽ ሚሊዮን ህዝብ ነው ከቀየው የተፈናቀለው። ስለምሥራቅ ኮንጎና ፤ ለጊዜው አልባት ስልልተደረገለት ውዝግብ ፤ ተክሌ የኋላ የሚከተለውን አጠር ያለ ዘገባ አጠናቅሯል።

የታላላቆቹ ሀይቆች አካባቢ መንግሥታት መሪዎች፤ በኮንጎ የተሠማሩትን አማጽያን  እንቅሥቃሴ ለማረቅ፤ ቀደም ሲል በተስማሙት  መሠረት ካምፓላ ፤ ዩጋንዳ ላይ ፣ ከማክሰኞ አንስተው እስከትናንት ለ 2 ቀናት ቢመክሩም፤ ስምምነት ላይ ሳይደርሱ ነበረ የተለያዩት። እንደሚባለው ከሆነ ውዝግቡ ውስብስብ ያለ በመሆኑ ፤ በላጋሽ አገሮች ግፊት ብቻ የሠመረ ውጤት ማግኘት መቻሉ ከመጀመሪያውም የተጠራጠሩ ነበሩ።

Uganda's President Yoweri Museveni (R) gestures during the closing ceremony of the International Conference on the Great Lakes Region (ICGLR) at the Commonwealth Resort Hotel Munyonyo in the capital of Kampala August 8, 2012. African leaders of the Great Lakes region say they will impose sanctions on any party obstructing peace in the volatile Democratic Republic of Congo on Wednesday. The decision was reached at the end of a two-day leaders summit on the conflict in Uganda. REUTERS/Edward Echwalu (UGANDA - Tags: POLITICS CIVIL UNREST)
ምስል Reuters
Rwanda's President Paul Kagame listens to deliberations during the International Conference on the Great Lakes Region (ICGLR) at the Commonwealth Resort Hotel Munyonyo in the Ugandan capital of Kampala August 8, 2012. African leaders of the Great Lakes region say they will impose sanctions on any party obstructing peace in the volatile Democratic Republic of Congo on Wednesday. The decision was reached at the end of a two-day leaders summit on the conflict in Uganda. REUTERS/Edward Echwalu (UGANDA - Tags: POLITICS CIVIL UNREST)
ምስል Reuters


የኮንጎ የማስታወቂያ ሚንስትር ላምቤ ሜንደ ግን ፤ ተስፋ በማድረግ እንዲህ ነበረ ያሉት፤
«የሚያሳዝነው ፤ ጎረቤቶቻችን የሩዋንዳ ነጻ አውጭ ኃይል (FDLR)የተሰኘውን እንጂ M 23 የተባለውን መውጋት አይገባም የሚል አቋም ነበረ የሚያራምዱት፤ ህዝቡ ግን በ FDLR ም በ M 23 ም ነው የሚገደለው። ስለሆነም ሁለቱንም ንቅናቄዎች ማጥፋት አለብን። ያም ሆነ ይህ አዲስ አበባ ላይ ጉዳዩ ተንቀሳቅሶ፤ ፕሬዚዳንት ካጋሜም m 23 ጭምር አሉታዊ ኤይል መሆኑን በደነገገው ሰነድ ላይ ፈርመዋል። እንድ በጎ እርምጃ አለ ማለት ነው።»
ግራም ነፈሰ ቀን፤ በካምፓላ ዓለም አቀፍ ጉባዔ የተገኙት የ 11 አባል ሃገራት ተጠሪዎች፤ ለውዝግቡ «አገር በቀል መላ » ለመፈለግ ተስማምተው ነው የተለያዩት። ከተጠቀሱት አገሮች መካከል የ 7,ቱ  ሃገራት የመከላከያ ሚንስትሮች፣ የሩዋንዳና የኮንጎ ዴሞክራቲክ  ሪፓብሊክ   ጭምር ፣ ምን ያህል ሰላም አስከባሪ ወታደሮች እንደሚያስፈልጉ የስንቅና ትጥቁንም  መጠን አስልተው ከ 4 ሳምንት በኋላ ለመሪዎቹ ጉባዔ የሚያቀርቡ መሆናቸውን የዩጋንዳው ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ አስታውቀዋል። የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታ ጥበቃው ም/ቤት ፣ በቱስሲዎች ለሚመራው M 23 ለተሰኘው አማጺ ኅይል ድጋፍ  መስጠት ይቁም ሲል ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ፣ ተግሳፁ ሩዋንዳንና ዩጋንዳን የሚመለከት እንደነበረ ተመልክቷል።
ሩዋንዳም ፤ ዩጋንዳም ለ M 23 መሣሪያም ሆነ የሚመለመሉ ወታደሮች አለማቅረባቸውን የገለጡት። ውዝግቡን ፣ ከታላላቆቹ  ሀይቆች አዋሳኝ ሀገራት የተውጣጡ ወታደሮች ፤ የM 23 ን እንቅሥቃሴ እንዲገቱ  ፕሬዚዳንት ጆሰፍ ካቢላ ቢስማሙም የመከላከያ ሚንስትሩ አሌክሳንደር ሉባ እንታምቦ ይህ እውነት ነው ሲሉ አለማረጋገጣቸውን ፤ የዩጋንዳው ውጭ ጉዳይ  ሚንስትር ሄንሪ ኦኬሎ ኦሪየም  ተናግረዋል።
በኮንጎ 17 ሺ የተባበሩት መንግስታት ሰላም አስከባሪ ጦር እንደተሠማራ የሚገኝ  ቢሆንም ወርቅ፤ መዳብ፣ ቆርቆሮ፣ አላማዝና ሌሎችም የከበሩ ማዕድናት የሚገኝባትን ግዙፍ ሀገር ፀጥታ ሙሉ በሙሉ ለማስከበር እንደተሳናቸው ነው የሚኙት። ለዚህም ነው ከአካባቢው መንግሥታት የተውጣጣ ኃይል በምሥራቅ ኮንጎ ሰላም እንዲያስከብር የተፈለገው።
የዩናይትድ እስቴትስ ውጭ  ጉዳይ ሚንስትር ሂልሪ ክሊንተን፤ ከትናንት በስቲያ፤ ሩዋንዳና ሌሎች የታላላቆቹ ሀይቆች አካባቢ መንግሥታት፣  M 23 ን ከመደገፍ እንዲቆጠቡ መጠየቃቸው የሚታወስ ነው። ለጋሽ መንግስታት፤ ዩናይትድ እስቴትስና ብሪታንያ፣ ኔደርላንድና ጀርመን ለሩዋንዳ የሚሰጡትን የገንዘብ  እርዳታ፤ አማጽያኑን ትደግፋለች በማለት በከፊል መቀነሣቸውን አስታውቀዋል። 

ተክሌ የኋላ

ሂሩት መለሰ