1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ የእርሻ ልማት ይዞታ

ረቡዕ፣ ጥር 8 2005

የአፍሪቃ አነስተኛ ገበሬ 80 በመቶውን የክፍለ-ዓለሚቱን ምግብና የእርሻ ምርት የሚያቀርብ ሲሆን ለተቀረውን ዓለም የምግብ ፍላጎትም ሰፊ አስተዋጽኦ ያደርጋል።

https://p.dw.com/p/17KRT
ምስል AP

የአፍሪቃ አነስተኛ ገበሬ 80 በመቶውን የክፍለ-ዓለሚቱን ምግብና የእርሻ ምርት የሚያቀርብ ሲሆን ለተቀረውን ዓለም የምግብ ፍላጎትም ሰፊ አስተዋጽኦ ያደርጋል። ይሄው አርሶ-አደር በአንጻሩ ከረሃብ ሳይላቀቅ በአስከፊ ድህነት የሚኖር ነው። ይሁንና አሁን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትንሹን ገበሬ ከዓለም ገበያ በማስተሳሰርና ምርታማ በማድረግ የኑሮ ሁኔታውን ለማሻሻል በተለያዩ ታላላቅ ኩባንያዎች፣ በመንግሥታትና ከመንግሥታት ነጻ በሆኑ ድርጅቶች ጥረት ተይዞ ነው የሚገኘው። ለዚሁ ጥረት አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ከሚገኙት ድርጅቶች አንዱ ደግሞ በአሕጽሮት CTA በሚል አሕጽሮት የሚጠራው ኔዘርላንድ-ግሮኒንገን ላይ ተቀማጭ የሆነ እርሻና የገጠር ልማትን በአፍሪቃ፤ ካራይብ- ፓሢፊክ አካባቢ ለማራመድ የሚሠራ የእርሻ ልማት ትብብር ቴክኒካዊ ማዕከል ሲሆን የተቋሙን ሃላፊ አቶ ሚካኤል ሃይሉን በጉዳዩ አነጋግሯል፤ ያድምጡ!

መሥፍን መኮንን

አርያም ተክሌ