1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ የወባ ቀን

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 17 1999

በአለማችን ዙርያ በአመት ሶስት ሚሊዮን ህዝብ በወባ በሽታ ህይወቱ እንደሚያጣ ከህም መካከል ዘጠና በመቶ ያህሉ የደቡባዊ አፍሪቃ ክልል ነዋሪዎች እንደሆኑ አለማቀፉ የጤና ጥበቃ ድርጅት አስታወቀ

https://p.dw.com/p/E0h7
የወባ ቀን በኢትዮጽያ ለ7ኛ ግዜ
የወባ ቀን በኢትዮጽያ ለ7ኛ ግዜምስል picture-alliance/dpa

በዛሪዉ እለት ኢትዮጽያ ዉስጥ ለሰባተኛ ግዜ የአፍሪቃን ወባ ቀን በማስመልከት ስለ በሽታዉ ግንዛቤ የሚሰጡ የተለያዩ ዝግጅቶች ተካሂደዋል። በኦሮማይ ክልላዊ መንግስት መቂ ከተማ በወባ በሽታ ተጠቂ መሆንዋን ዶክተር ዘሪሁን ታደሰ በፊደራል ጤና ጥበቃ ሚ/ር የበሽታዎች መከላከያ እና መቆጣጠርያ መምርያ ሃላፊ ገልጸዉልናል። በመቂ ከተማ የተካሄደዉን ዝግጅት እና በኢትዮጽያ በመካሄድ ላይ ስላለዉ የወባ መከላከያ ፕሮግራም ባለሞያ አነጋግረናል