1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

   የኢትዮጵያዉያን መንገላታት እና አምባሳደሩ

ዓርብ፣ ሰኔ 30 2009

በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን በሰነድና በመጓጓዣ እጦት መንገላታታቸዉን በተደጋጋሚ ሲገልጡ ነበር።

https://p.dw.com/p/2gALp
Amin Abdulkadir
ምስል DW/S. Shiberu

Beri.Riyadh) Äth.Botschafter in Saudi Arabia - MP3-Stereo

የሳዑዲ ዓረቢያ መንግስት ሕገ-ወጥ ያላቸዉ የዉጪ ዜጎች ከሐገሩ እንዲወጡ በሰጠዉ የጊዜ ገደብ ወደ ሐገራቸዉ መግባት በፈለጉ ኢትዮጵያዉያን ላይ ደርሶ የነበረዉ መንገላታት መቃለሉን በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አሚን አብዱልቃድር አስታወቁ።በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን በሰነድና በመጓጓዣ እጦት መንገላታታቸዉን በተደጋጋሚ ሲገልጡ ነበር።የሳዑዲ አረቢያ መንግስት የጊዜ ገደቡን ባንድ ወር ቢያራዝምም ወደ ሐገራቸዉ መመለስ የፈለጉ ኢትዮጵያዉያን አሁን በመጓጓዢያ እጦት አዉሮፕላን ማረፊያዎች፤በኢትዮጵያ ኮሙኒቲ አዳራሽና በየሰዉ ቤት ለመጠለል ተገድደዋል።አምባሳደር አሚን ተመላሾች በቀረዉ ጊዜ ዉስጥ ለጉዞ እንዲዘጋጁ መክረዋል።

ስለሺ ሽብሩ 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ