1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ተቃዉሞ በለንደን

ዓርብ፣ ነሐሴ 24 2005

ብሪታንያ የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵዮዉያን በዛሬዉ ዕለት ሎንደን ላይ የተቃዉሞ ሰልፍ አካሄዱ።

https://p.dw.com/p/19ZF9
ምስል DW/H. Demissie

ተሰላፊዎቹ ሰላማዊ ትግሉ ይቀጥላል፤ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሙስሊሞች መብት ይከበር፤ ኢትዮጵያ የሁሉም ሃይማኖት ሀገር ናት የሚሉ መፈክሮች ሲያሰሙ እንደነበር ተገልጿል። ሰልፉ የተካሄደዉ በእንግሊዝ የፓርላማ አደባባይ ከፓርላማዉ ፊት ለፊት ሲሆን በስፍራዉ ተገኝታ ሁኔታዉን በተከታተለችዉ ዘጋቢያችን ሃና ደምሴ ግምት ከሁለት መቶ በላይ ሰልፈኞች ተገኝተዋል። ወደሎንዶን ደዉዬ ሰልፉ በሚካሄድበት ሰዓት እዚያ የተገኘችዉን ሃናን እና ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱን ስለሁኔታዉ አነጋግሬያለሁ፤

ሃና ደምሴ

ሸዋዬ ለገሠ

አርያም ተክሌ