1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያዊነት ውርስ እና ቅርስ ማህበረሰብ ክብረ በዓል

ሰኞ፣ ሐምሌ 20 2007

የኢትዮጵያዊነት ውርስ እና ቅርስ ማህበረሰብ ዕሁድ ዕለት አምስተኛውን ክብረ በዓል በሰሜን አሜሪካ አክብሯል። በዚሁ ዕለት ኢትዮጵያውያን ፣ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ የኢትዮጵያ ወዳጆች እና ተጋባዥ እንግዶች መገኘታቸውን ከዋሽንግተን ዲሲ የደረሰን ዘገባ ያስረዳል።

https://p.dw.com/p/1G5L5
Deutschland Jahrestag Etemete - Deutsch-äthiopische Kultur und Familien e.V.
ምስል Samuel Tesfaye

[No title]

ይህ ድርጅት፤ የቀድሞ ታሪክና ቅርፅን በመጠበቅ ለአሁኑ ትውልድ እና ለመጪው በክብር የማስተላለፍ ዓላማን ሰንቆ ይንቀሳቀሳል። የዘንድሮው ዝግጅት በተለይ በሊቢያ እና በደቡብ አፍሪቃ በግፍ ለተገደሉ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን መታሰቢያ እንደሆነም ተገልጿል። ከዋሽንግተን ዲሲ እና ሜሪላንድ ክፍለ ግዛቶችም ለበዓሉ እውቅና የሰጠ የምስክር ወረቀቶችም ተበርክቷል።

መክብብ ሸዋ

ልደት አበበ

ሸዋዬ ለገሠ