1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ሙስሊም መሪዎች የፍርድ ሒደት

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 3 2006

የኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት ጥርጣሬ ካሰራቸዉ የኢትዮጵያ የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎች፥ አባላትና ተባባሪዎች መካካል አስራ-ሁለቱ በነፃ እንዲለቀቁ ተወሰነ።

https://p.dw.com/p/1AYAL
ምስል picture-alliance/dpa

ዛሬ አዲስ አበባ ያስቻለዉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት በነፃ ካሰናበታቸዉ ተከሳሾች መካካል የቀድሞዉ የሲቪል ሠርቪስ ሚንስትር የአቶ ጁኔዲ ሳዶ ባለቤት እና ሁለት ድርጅቶች ይገኙባቸዋል።የተከሳሾቹ ጠበቃ አቶ ተማም አባቡልጋ እንደገለፁት ፍርድ ቤቱ በሌሎቹ ተጠርጣሪዎች ላይ የተያዘዉን የወንጀል ጭብጥም «ከአሸባሪነት» ወደ «ሽብር አነሳሽነት» እና ተባባሪነት አቅልሎላቸዉል።የቀሪዎቹን ጉዳይ ለማየት ፍርድ ቤቱ ለመጪዉ ጥር ሃያ-ሁለት ቀጠሯል። አቶ ተማምን ነጋሽ መሐመድ በስልክ አነጋግሯቸዋል።

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ