የኢትዮጵያ አቋም፣ ተመድና የትግራይ ግጭት
ዓርብ፣ ሐምሌ 2 2013ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የምታስገነባዉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ከእንግዲሕ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታዉ ምክር ቤት መነጋገሪያ ርዕሥ እንደማይሆን የሐገሪቱ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር አስታወቀ። በሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሠበብ ኢትዮጵያ ከግብፅና ሱዳን ጋር ስለገጠመችዉ ዉዝግብ የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት ትናንት ባደረገዉ ዉይይት አስተያየት የሰጡት የምክር ቤቱ አባላት ሶስቱ ሐገራት ልዩነታቸዉን ለማስወገድ በአፍሪቃ ሕብረት ሸምጋይነት እንዲደራደሩ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት አብዛኞቹ የምክር ቤቱ አባል ሐገራት ተወካዮች ከቃላት ልዩነት በስተቀር ጉዳዩ ወደ አፍሪቃ ሕብረት እንዲመለስ ተናግረዋል። አምባሳደር ዲና ትግራይ ዉስጥ ያለዉን ወታደራዊ ቀዉስ በተመለከተ በሰጡት መግለጫም «የሕወሓት አማፂ ቡድን ሰበረዉ» ያሉትን የተከዜ ድልድይን ለመጠገን መንግስታቸዉ እየጣረ መሆኑን አስታዉቀዋል።ሳዑዲ አረቢያ ከሐገሯ እንዲወጡ ከወሰነችባቸዉ ኢትዮጵያን መካከል ከ21 ሺሕ የሚበልጡ ሐገራቸዉ መግባታቸዉን ገልፀዋልም።
ሠለሞን ሙጬ
ነጋሽ መሐመድ
እሸቴ በቀለ