1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት መግለጫ

ረቡዕ፣ ሰኔ 3 2007

የፓርቲው ፕሬዝዳንት አቶ አድማሱ ኃይሉ ከዶቼቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ምርጫው ነፃና ዲሞክራሲያዊ ስላልሆነ ፓርቲያቸው እንደማይቀበለው ተናግረዋል ።

https://p.dw.com/p/1FejN
Addis Ababa (Äthiopien)
ምስል picture alliance/landov

[No title]


የኢትዮጵያ አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት የተሰኘዉ ተቃዋሚ ፓርቲ ባለፈዉ ግንቦት 16 የተደረገዉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ነፃና ፍትሃዊ አልነበረም ሲል አስታወቀ ።የፓርቲው ፕሬዝዳንት አቶ አድማሱ ኃይሉ ከዶቼቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ምርጫው ነፃና ዲሞክራሲያዊ ስላልሆነ ፓርቲያቸው እንደማይቀበለው ተናግረዋል ።አቶ አድማሱ እንዳሉት በዕጩዎች ምዝገባ በምርጫ ቅስቀሳና በምርጫውም ወቅት የፓርቲያቸው አባላት እጩዎቻቸውና ታዛቢዎቻቸው ወከባና እንግልት ደርሶባቸዋል ። ከዛሬ 16 ዓመት በፊት የተመሰረተው የኢትዮጵያ አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በ1997ቱና በ2002ቱ ምርጫም ተካፍሏል ። አቶ አድማሱን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሬያቸዋለሁ ።

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሀመድ