1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ አይሁዳውያን መታሰቢያ በእሥራኤል

ረቡዕ፣ ግንቦት 27 2006

እአአ በሰማንያኛዎቹ ዓመታት በሱዳን በኩል አድረገው ወደ እሥራኤል ለመሄድ ሲሞክሩ በጉዞ ላይ ለሞቱት የኢትዮጵያ አይሁዳውያን በሄርዝል ተራራ በቆመው የመታሰቢያ ሐውልት በያመቱ በሚደረገው ሥነ ሥርዓት ላይ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የ1,500ዎቹ ስም በሐውልቱ ላይ ተቀረጸ።

https://p.dw.com/p/1CBsy
ምስል DW/K. Shuttleworth

ለሟቾቹ መታሰቢያ እንዲሰራ ሰፊ ድርሻ ያበረከተው የቤተ እሥራኤላውያኑ ድርጅት ይኸው ርምጃ እንዳስደሰተው ቢገልጽም፣ የሁሉም ሟቾች ስም በሐውልት ላይ ባለመቀረጹ ቅር መሰኘታቸውን አስታውቀዋል። በዚሁ ጉዞ ሕይወታቸው የጠፋው ሰዎች ቁጥር 4,000 እንደሚሆን በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ ጠበብት ይገምታሉ። የእሥራኤል ፕሬዚደንት ሺሞን ፔሬስ፣ ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፣ እንዲሁም፣ ከፍተኛ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት እና የምክር ቤት አባላት ስለተገኙበት ስለዚሁ ልዩ ሥነ ሥርዓት የሀይፋ ወኪላችን ግርማው አሻግሬ የድርጅቱን ፕሬዚደንት አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

ግርማው አሻግሬ

አርያም ተክሌ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ