የኢትዮጵያ ኢኮኖሚና የዓለም ባንክ
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 11 2005ማስታወቂያ
የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ መንግሥት ለነደፈዉ የአምስት ዓመት የዕድገትና የለዉጥ ዕቅድ ድጋፍ መስጠቱን እንደሚቀጥል አስታወቀ።የባንኩና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት አዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል ባደረጉት ዉይይት ላይ እንደተገለጠዉ ዓለም አቀፉ አበዳሪ ተቋም «ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት አሳያች» ባለዉ የምጣኔ ሐብት ዕድገት ረክቷል።ባንኩ እስካሁን የሚያደርገዉን ድጋፍ በሚቀጥሉት ሰወስት ዓመታትም መስጠቱን ይቀጥላል።የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ግን አድጓል የሚባለዉ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሐብት የሕዝቡን ኑሮ ይበልጥ ከማክበድ ሌላ የጠቀመዉ ነገር የለም ባዮች ናቸዉ።ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።
ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ