1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የሰብዓዊ መብት ይዞታ

ዓርብ፣ ግንቦት 5 2003

ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል በ 89 አገራት የመናገር መብት መገፈፉን አስታወቀ።

https://p.dw.com/p/RNqs
ምስል AP/DW-Grafik

ድርጅቱ በዓለም ዙሪያ በበርካታ አገራት የሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ባጋለጠበት ዓመታዊ ዘገባው በ 98 አገራትም እስረኞች የሚገረፉና የሚንገላቱ መሆናቸውን እንዲሁም በ 48 አገራት ደግሞ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ የሚያሰሙ ሰዎች እንደሚታሰሩና እንደሚንገላቱ ይፋ አድርጓል ። አምነስቲ በሰብዓዊ መብት ረገጣ ከከሰሳቸው አገራት ውስጥ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ይገኙበታል ። የለንደኑ ዘጋቢያችን ድልነሳ ጌታነህ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ስለ ሁለቱ አገራት ስላወጣው ዘገባ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ እና የኤርትራ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ሃላፊዎችን አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል ።

ድልነሳ ጌታነህ

ተክሌ የኋላ

ሂሩት መለሠ