1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ወታደሮች መዉጣትና የሶማሊያ እጣ

ሰኞ፣ ኅዳር 22 2001

ላለፉት 17ዓመታት በግጭትና ጦርነት የታጀበ ህይወት እየገፋ የሚገኘዉ የሶማሊያ ህዝብ ቀጠሮ አልባ ጥቃቶች ቢደርሱም ኑሮዉን ኑሮ ብሎ እየገፋዉ ነዉ።

https://p.dw.com/p/G6zh
ታጣቂዎቹ ጉዞ ወደመቃዲሾ
ታጣቂዎቹ ጉዞ ወደመቃዲሾምስል AP

ሰሞኑን የኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮቹን ከሶማሊያ ለማዉጣት መወሰኑ በአንዳንድ ሶማሌዎች ዘንድ የጥቃት በትር እንዲቀንስ ያደርጋል የሚል ተስፋን አሳድሯል። እስላማዊ ኃይሎቹ ተጠናክረዉ በሚገኙበት በዚህ ወቅት የተወሰደዉ ርምጃ የሚፈጥረዉን የፀጥታ ክፍተት እያሰቡ የሚሰጉ ወገኖችም አልታጡም።