1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተመድ አስተያየት

ሐሙስ፣ ጥቅምት 24 2009

በተመድ የፖለቲካ ጉዳዮች ተጠሪ ሆዜ ሉስየስ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ድርጅታቸው ኢትዮጵያ ከሶማልያ ወታደሮችዋን እንደምታስወጣ አስቀድሞ አልተነገረውም ።

https://p.dw.com/p/2S5vu
Somalia Islamisten fliehen aus somalischer Hafenstadt Kismayo
ምስል picture-alliance/ dpa

Beri Wash.(UN rxn on Ethiopian troops withdrawal from Somalia) - MP3-Stereo

ኢትዮጵያ ወታደሮቿን ከሶማሊያ ስታስወጣ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዳላሳወቀች ተነገረ ። በተመድ የፖለቲካ ጉዳዮች ተጠሪ ሆዜ ሉስየስ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ድርጅታቸው ኢትዮጵያ ከሶማልያ ወታደሮችዋን እንደምታስወጣ አስቀድሞ አልተነገረውም ። የቀድሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ኢትዮጵያ  በራስዋ ወጭ ሶማሊያ ያዘመተቻቸውን ወታደሮቿን በገንዘብ ችግር ምክንያት እንዳስወጣች ባለፈው ሳምንት ተናግረው ነበር ። የመንግሥታቱ ድርጅት ባለሥልጣን ሉስየስ እንዳሉት ድርጅታቸው  የኢትዮጵያ ወታደሮች በመውጣታቸው የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት ሌሎች አባላትን እየጠየቀ መሆኑን አስታውቀዋል ።

መክብብ ሸዋ

ኂሩት መለሰ

አዜብ ታደሰ