1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢጣልያ የፖለቲካ ይዞታ

ሐሙስ፣ መስከረም 23 2006

ኤኮኖሚዋ የዕድገት እንቅሥቃሴ አላሳይ ብሎ፤ በሥራ አጦች መበራከትና በበጀት ዕዳ የተወጠረችው ኢጣልያ፤ እነዚህን ችግሮች መፍታት የሚችል የተደላደለ መንግሥት ማቆም አቅቷት ስትዋትት ከቆየች በኋላ ፣

https://p.dw.com/p/19tOe
Italy's Prime Minister Enrico Letta (C), flanked by Interior Minister Angelino Alfano (R) and Democratic Party (PD) member Dario Franceschini, addresses the Senate asking for a possible call for a confidence vote immediately in Rome, October 2, 2013. Senior party figures in Silvio Berlusconi's fractious centre-right movement urged Italian lawmakers on Tuesday to defy the billionaire media tycoon and back Letta in a confidence motion expected on Wednesday. REUTERS/Tony Gentile (ITALY - Tags: POLITICS)
ምስል Reuters

ኤኮኖሚዋ የዕድገት እንቅሥቃሴ አላሳይ ብሎ፤ በሥራ አጦች መበራከትና በበጀት ዕዳ የተወጠረችው ኢጣልያ፤ እነዚህን ችግሮች መፍታት የሚችል የተደላደለ መንግሥት ማቆም አቅቷት ስትዋትት ከቆየች በኋላ ፣ በመጨረሻ በመኻል ቀኝ ፈለግ ተከታዩ ፓርቲና በመኻል ግራ ፈለግ ተከታዩ ፓርቲ ጥምረት ፣ የሀገርን ጥቅም ለማስቀደም የተመሠረተው በጠ/ሚንስትር ኤንሪኮ ሌታ የሚመራው መንግሥት ፣ ትናንት ለጥቂት ነው ከመፍረስ የዳነው። ይህም ሊሆን የቻለው ፣ የቀድሞው ጠ/ሚንስትር ሲልቪዮ ቤርሉስኮኒ የፓርቲአቸውን ሰዎች አግባብተው ፣ በምክር ቤቱ ፤ ለሌታ ድጋፍ እንዳይሰጥ ያካሄዱት ዘመቻ፤ አንጀሊኖ አላፋኖ በተባሉት የራሳቸው ፓርቲ ባልደረባ መሪነት የቤርሉስኮኒ ሃሳብ ተቀባይነት ሳያገኝ በመቅረቱ ነው። የኢጣልያን ወቅታዊ ፖለቲካ በተመለከተ የብራሰልሱን ዘጋቢአችንን ገበያው ንጉሤን በስልክ አነጋግሬው ነበር።

ገበያው ንጉሤ

ተክሌ የኋላ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ