1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኤርትራዉያን ሰልፍ ትኩረት

ሰኞ፣ የካቲት 8 2002

የተመድ በኤርትራ መንግስት ላይ የጣለዉን ማዕቀብ የሚቃወም ዓለም ዓቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ የፊታችን ሰኞ በኤርትራዉያን መጠራቱ እየተነገረ ነዉ።

https://p.dw.com/p/M1mB
ምስል AP

ድርጅቱ ኤርትራ በሶማሊያ ለሚንቀሳቀሱ ፅንፈኛ ታጣቂዎች የመሳሪያ ርዳታ ታደርጋለች ሲል ይከሳል። የኤርትራ መንግስት ክሱን በማጣጣል ማዕቀቡ በአገሪቱ ጠላቶች የተቀነባረ መሆኑን ተናግሯል። በአንፃሩ ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ መብቶች ለኤርትራ የተሰኘዉ የኤርትራዉያን የሲቪክ ድርጅት ይህን ማዕቀብ በመቃወም የተጠራዉ ሰልፍ በአገሪቱ ዉስጥ ባሉ የፖለቲካ ችግሮች ላይ እንዲያተኩር ጠይቋል። የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሤ ዘገባ አድርሶናል።

ገበያዉ ንጉሤ/ሸዋዬ ለገሰ

አርያም ተክሌ