1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኤርትራዉያን ስደት ዘጋቢ ፊልም

ዓርብ፣ መስከረም 30 2007

ባለፈዉ ዓመት540 ሰዉ የጫነት አንዲት ጀልባ በሜዲትራኒያን ባህር ዉስጥ ስትሰጥም ወደአራት መቶ የሚሆኑት ህይወታቸዉ ማለፉ ይታወሳል። ሁኔታዉን አሳፋሪ የታሪክ ጥላሸት ሲሉ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ተችተዉታል። የእሳቸዉን አባባልም አብዛኞች ደግመዉታል።

https://p.dw.com/p/1DTLa
Italien Flüchtlinge aus Palästina und Syrien 07.08.2014
ምስል picture alliance/ROPI

ክስተቱ በወቅቱ የዓለም መገናኛ ብዙሃንን ከፍተኛ ትኩረት ለቀናት ይዞ ቆይቷል። ከሊቢያ የባህር ወደብ ወደአዉሮፓ ለመግባት በጀልባ ተጭነዉ የመጡ አብዛኞቹ ኤርትራዉያን የሆኑበት ጉዞ ካለሙት ሳይደርሱ ባህር ዉስጥ ማለቃቸዉ ብዙዎችን ከማሳዘን አልፎ መንስኤዉን እንዲያጤኑ ጋብዟል። ሁለት የጀርመን ARD ቴሌቪዥን ጋዜጠኞችም ኤርትራ ሄደዉ ስደተኞቹ የተጓዙበትን 3,000 ኪሎ ሜትር በፊልም ቀርጸዉ እዉነታዉን በዘጋቢ ፊልም ለተመልካች አቅርበዋል። ፊልሙን የተመለከተዉ የበርሊን ዘጋቢያችን ይልማ ኃይለ ሚካኤል ጋዜጠኞቹን በማነጋገር ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ