1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የእስራኤልና ሃማስ ተኩስ አቁም

ሐሙስ፣ ኅዳር 13 2005

ሁለቱ ወገኖች ተኩስ ለማቆም የተስማሙት በግብፅና በአሜሪካን የሽምግልና ጥረት ነው ። ስምምነቱም በመነጋገር በቃል የፀና እንጂ በፊርማ የፀደቀ አይደለም ። ሁለቱም ወገኖች ለተኩስ አቁም የሚያስፈልጉትን ቅድመ ግዴታዎች ካሟሉ ከ 24 ሰዓትት በኋላ በነርሱ ጥያቄ በሃምስና በእስራኤል መካከል ድርድር ሊጀመር ይችላል ።

https://p.dw.com/p/16oJh
epa03480771 US Secretary of State Hillary Rodham Clinton (L) and Egyptian Foreign Minister Mohammed Kamel Amr (R) are seen during a joint press conference, in Cairo, Egypt, 21 November 2012. Media reports state that Egyptian Foreign Minister Mohammed Kamel Amr said a ceasefire agreement has been reached between Israel and Hamas after eight days of fighting. The truce is to commence at 1900 GMT. EPA/KHALED ELFIQI +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture alliance/dpa
Palestinians celebrate the cease fire agreement between Israel and Hamas in the Jebaliya refugee camp, in Gaza Strip, Wednesday, Nov. 21, 2012. Israel and the Hamas militant group agreed to a cease-fire Wednesday to end eight days of the fiercest fighting in nearly four years, promising to halt attacks on each other and ease an Israeli blockade constricting the Gaza Strip. (Foto:Hatem Moussa/AP/dapd)
ምስል AP
Israeli soldiers, atop a tank, prepare to leave their Gaza border position at sun rise November 22, 2012. A ceasefire between Israel and Gaza's Hamas rulers took hold on Thursday after eight days of conflict, although deep mistrust on both sides cast doubt on how long the Egyptian-sponsored deal can last. REUTERS/Yannis Behrakis (ISRAEL - Tags: CONFLICT POLITICS)
ምስል Reuters
Pro-Palestinian demonstrators stand next to candles during a protest against the Israeli offensive in Gaza on November 21, 2012 in front of the United Nations Office in Geneva. A ceasefire agreed between Israel and Hamas officially came into effect on the basis of the text of the deal announced shortly beforehand in Egypt. AFP PHOTO / FABRICE COFFRINI (Photo credit should read FABRICE COFFRINI/AFP/Getty Images)
ምስል FABRICE COFFRINI/AFP/Getty Images

እስራኤልና ሃማስ የተስማሙበት ተኩስ አቁም እንዲከበር ተጠየቀ ። ጋዛን የሚያስተዳድሩት የሃማስ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢስማኤል ሃንያ የተለያዩ የፍልስጤም አንጃዎች ለስምምነቱ ተገዥ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል ። ሃንያ መልዕክቱን ያስተላለፉት በተኩስ አቁም ስምምነቱ መሠረት ሃማስ በፍልስጤም ምድር የሚንቀሳቀሱ ሌሎች የሚሊሽያ ቡድኖች ተኩስ አቁሙን እንዲያከብሩ በተጣለበት ሃላፊነት መሠረት ነው ። ስምምነቱ ለፍልስጤማውያን እንደ ድል ተቆጥሯል ። አንዳንድ እስራኤላውያን ደግሞ በነታንያሁ ውሳኔ አልተደሰቱም ።
8 ቀናት ከዘለቀው የእስራኤል የጋዛ ድብደባና የፍልሴማውያን የሮኬት ተኩስ በኋላ እስራኤልና ሃማስ ተኩስ ለማቆም መስማማታቸው ትናንት ማምሻውን ይፋ የተደረገው ከእየሩሳሌም ወይም ከራማላህ ሳይሆን ከካይሮ ግብፅ ነበር ። የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መደረሱ እንደተገለፀም ፍልስጤማውያን ደስታ ፈንቅሏቸው በጋዛ ጎዳናዎች ሲጨፍሩ አምሽተዋል ። ደሰታቸውን ለመግለፅም ከ 1ሺህ ጊዜ በላይ ወደ ሰማይ መተኮሳቸውም ተዘግቧል ። ደሰታቸውን ለመግለፅም  እንደ ድል የቆጠሩት የተኩስ አቁም ስምምነት እፎይታን አስገኝቶላቸዋል ። የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ነታንያሁ መንግስታቸው ስምምነቱን መቀበሉን ሲገለፅ ትንኮሳው ከቀጠለ እስራኤል በዝምታ የምታልፈው አለመሆኑን ተናግረዋል  ።

የአሁኑ የስምምነቱ ፣እስራኤል ሰርጎ ገብ እንቅስቃሴን እንዲሁም ግለሰቦችን ለይቶ ማጥቃትን ጨምሮ ከምድር ከአየር ም ሆነ ከባህር ማንኛውንም ትንኮሳና ወደ ግጭት የሚያመራ እርምጃ እንዳትወስድ ይጠይቃል ። ፍልስጤማውያን አንጃዎችም የጓዳ ሰራሽ ሮኬቶች ጥቃትን እንዲያቆሙና ድንበር አካባቢም ከሚፈፅሙት ማናኛውም ጥቃት እንዲቆጠቡ ጥሪ ያደርጋል ። ሁለቱ ወገኖች ተኩስ ለማቆም የተስማሙት በግብፅና በአሜሪካን የሽምግልና ጥረት ነው ። ስምምነቱም በመነጋገር በቃል የፀና እንጂ በፊርማ የፀደቀ አይደለም ። ሁለቱም ወገኖች ለተኩስ አቁም የሚያስፈልጉትን ቅድመ ግዴታዎች ካሟሉ ከ 24 ሰዓትት በኋላ በነርሱ ጥያቄ በሃምስና በእስራኤል መካከል ድርድር ሊጀመር ይችላል ።  እስራኤል ለምሳሌ ያህል ከጋዛ በኩል ጥቃት መሰንዘሩ እንዲቆም ብቻ ሳይሆን በፍልስጤም ግዛት የመቆጣጠር ሥልጣን አሁንም ሊኖረኝ ይገባል ነው የምትለው ። ሃማስ ደግሞ  እስራኤልና ግብፅ በጋዛ ላይ የተደረገው ከበባ እንዲነሳ እንዲያደርጉ እንዲሁም ሰዎችና እቃዎች ያለ ገደብ እንዲጓጓዙ ነው የጠየቀው ። በጋዛ የሚኖሩ ፍልስጤማውያን ድርድሩን አስመልክተው በሰጡት የመጀመሪያ አስተያየት እነርሱን ሊያረካቸው የሚችል ዘላቂ መፍትሄ መሆኑን ተናግረዋል ።
« የእስራኤልን ጦር አንፈራም ። ሆኖም ለሞቱትና ለሚፈናቀሉት ልጆቻችን ስንል ነው የተኩስ አቁሙ እንዲደረግ የምንፈልገው ። ለልጆቻችን ስንል ብቻ»
እስራኤልና ፍልስጤማውያንን ለመሸምገል ትናንት እየሩሳሌም ራማላ ና ካይሮ የነበሩት የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሂለሪ ክሊንተን በሽምግልናው ግብፅ አግዘዋል ። በስተመጨረሻ ከካይሮ ነበር ክሊንተን ወደ አገራቸው ያቀኑት ። እስራኤል እግረኛ ወታደሮቿን ወደ ጋዛ የመላክ እቅዷ እንዳለ ነው ። ይሁንና የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ኤሁድ ባራክ ተጨማሪ ውጊያ ከእንግዲህ ማካሄዱ ምክንያት ያለው ሆኖ አይታያቸውም ።
«ግቦቻችንን ሙሉ በሙሉ መተናል ። ሃማስና ኢስላማዊ ጂሃድ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ። የሃማስ ወታደራዊ አዛዥ ድሃሽባሪና ሌሎችም ከፍተኛ አዛዦችና የሃማስ አስተሳሰብ አራማጆች እንዲሁም በርካታ አሸባሪዎች ተገድለዋል ።
በአጠቃላይ ከ130 በላይ ተገድለዋል ። ከ 900 በላይ ቆስለዋል»  
ምንም እንኳን የ 8 ቀኑ ጦርነት ብዙ የሰው ህይወትና ንብረት ቢያጠፋም የተኩስ አቁምን ስምምነቱን ፍልስጤማውያን እንደ ድል ነው የቆጠሩት ። ከፍልስጤም ምድር የሚተኮሱት ሮኬቶች ቴላቪቭና እየሩሳሌምን መድረስ መቻላቸው በፍልስጤማውያን ዘንድ ለእስራኤል መንበርከክ ምክንያት ተደርጎ ነው የተወሰደው ። አንዳንድ እስራኤላውያን ደግሞ ነታንያሁ የተኩስ አቁሙን መቀበላቸውን ከውርደት ቆጥረውታል ። አንዳንድ ወታደሮች ጭምር የነተንያሁ እርምጃ አላስደሰታቸውም ። 

 

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ