1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታ

ማክሰኞ፣ የካቲት 24 2007

የኢትዮጵያ መንግሥትን የሚቃወሙ 6 የኦሮሞ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በድሎናል ሲሉ አማረሩ ። የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን ያልተፈታ ችግር እንደሌለና በተለይ በአባላት ላይ ይደርሳል ስለተባለው እንግልት ቦርዱ እንዳልሰማ ተናግረዋል ።

https://p.dw.com/p/1EkW7
Büro des National Electoral Board of Ethiopia NEBE
ምስል DW

ፓርቲዎቹ ከዚህ ቀደም ከተደረሰበት ስምምነት ውጭ አባላቶቻቸው እንደሚንገላቱ የበጀት ድጎማ እንደማይሰጣቸውና ለምርጫ ቅስቀሳ አመቺ የአየር ጊዜ እንደተነፈጉ ተናግረዋል ። ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን ያልተፈታ ችግር እንደሌለ ተናግረዋል። በጀትን በተመለከተ ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች በሙሉ በእኩል የሚካፈፈለው ገንዘብ ሰሞኑን እንደሚለቀቅ አስታውቀዋል ።ሁለቱንም ወገኖች ያነጋገረው የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል ።

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ