1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኦነግ አባላት እጅ መስጠት

ሰኞ፣ ጥር 10 2002

የጦር ትጥቃቸዉን አስቀምጠዉ እጃቸዉን ለመንግስት መስጠታቸዉ የተነገረዉ የኦሮሞ ነፃ አዉጭ ግንባር አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የመንግስት መገናኛ ብዙሃንን ዋቢ ያደረገዉ የሮይተርስ ዘገባ አመለከተ።

https://p.dw.com/p/LYuv
ምስል AP

መሣሪያዎቻቸዉን ጨምረዉ እጃቸዉን የሰጡት የኦነግ ታጣቂዎች ከአንድ መቶ እንደሚልቁ ተነግሯል። ለሁለት የመከፈል ችግር የገጠመዉ የኦነግ አመራር አካላት በበኩላቸዉ እጃቸዉን ሰጡ የሚባሉት ታጣቂዎች ከግንባሩ ከተሰናበቱ አንድ ዓመት እንዳለፋቸዉ ይናገራሉ።

ሸዋዬ ለገሠ / ሂሩት መለሰ