1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የካይሮው የእስራኤል ኤምባሲ ዳግም መከፈት

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 6 2004

ከ 3 ወር በፊት በግብፅ ተቃዋሚዎች ጥቃት ከደረሰበት በኋላ የተዘጋው ካይሮ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ በቅርቡ እንደገና ተከፍቷል ።

https://p.dw.com/p/13UXe
Egyptian activists celebrate as they demolish a concrete wall built around a building housing the Israeli embassy in Cairo, Egypt, to protect it against demonstrators Friday, Sept. 9, 2011. Hundreds of Egyptian protesters tore down parts of a graffiti-covered security wall that had recently been put up near the entrance of the Israeli Embassy in Cairo. Egyptian security forces did not intervene as crowds climbed the embassy security wall, pummeled it with hammers and tore away large sections of the barrier. (Foto:Khalil Hamra/AP/dapd)
በካይሮው ኤምብሲ ላይ ጥቃት ሲሰነዘርምስል dapd

በወቅቱ ግብጽን ለቀው የወጡትን የእስራኤል አምባሰደር የተኩት አዲሱ የእስራኤል አምባሳደርም በዚህ ሳምንት ሰኞ ካይሮ ገብተዋልል ። ባለፈው ወር የስራ ጊዜያቸውን የፈፀሙትን ይስሃቅ ሌቫኖንን የተኩት አምባሳደር ያኮቭ አሚታይ በቅድሚያ ከሚያከናውኑት ተግባር አንዱ ለኤምባሲያቸው ደህንነቱ የተጠበቀ አካባቢ መፈለግ መሆኑ ይገመታል ። የእስራኤል ወታደሮች በመስከረም ወር ለፍልስጤም ሚሊሽያዎች ባለሙት ጥቃት 6 የግብፅ ድንበር ጠባቂ ፖሊሶች ከተገደሉ በኋላ ነበር በካይሮው የእስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት የተሰነዘረው ። የእስራኤል የሃይፋውን ወኪላችንን ግርማው አሻግሬን በጥቃቱ ምክንያት የለዘበ ስለ መሰለው የግብፅና እስራኤል ግንኙነት እንዲሁም ስለ እስራኤል የደህንነት ስጋት በስልክ ጠይቄዋለሁ ። ግርማው ኤምባሲው እንደገና ሊከፈት የቻለበትን ሁኔታ በማስረዳት ይጀምራል ።

ግርማው አሻግሬ

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ