የካይሮው የእስራኤል ኤምባሲ ዳግም መከፈት
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 6 2004ማስታወቂያ
በወቅቱ ግብጽን ለቀው የወጡትን የእስራኤል አምባሰደር የተኩት አዲሱ የእስራኤል አምባሳደርም በዚህ ሳምንት ሰኞ ካይሮ ገብተዋልል ። ባለፈው ወር የስራ ጊዜያቸውን የፈፀሙትን ይስሃቅ ሌቫኖንን የተኩት አምባሳደር ያኮቭ አሚታይ በቅድሚያ ከሚያከናውኑት ተግባር አንዱ ለኤምባሲያቸው ደህንነቱ የተጠበቀ አካባቢ መፈለግ መሆኑ ይገመታል ። የእስራኤል ወታደሮች በመስከረም ወር ለፍልስጤም ሚሊሽያዎች ባለሙት ጥቃት 6 የግብፅ ድንበር ጠባቂ ፖሊሶች ከተገደሉ በኋላ ነበር በካይሮው የእስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት የተሰነዘረው ። የእስራኤል የሃይፋውን ወኪላችንን ግርማው አሻግሬን በጥቃቱ ምክንያት የለዘበ ስለ መሰለው የግብፅና እስራኤል ግንኙነት እንዲሁም ስለ እስራኤል የደህንነት ስጋት በስልክ ጠይቄዋለሁ ። ግርማው ኤምባሲው እንደገና ሊከፈት የቻለበትን ሁኔታ በማስረዳት ይጀምራል ።
ግርማው አሻግሬ
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ