1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኮሬ ማኅበረሰብ አባላት አቤቱታ

ሰኞ፣ መጋቢት 30 2011

የታጠቁ ቡድኖች በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ በሚገኙ የኮሬ ማኅበረሰብ አባላት ላይ ግድያ እየፈጸሙ እንደሚገኙ የማኅበረሰቡ አባላት አስታወቁ።

https://p.dw.com/p/3GTKL
Teilnehmer und Mitglieder des 11. EPRDF-Kongresses treffen in Hawasa ein.
ምስል DW/Y. Geberegziabeher

የማኅበረሰቡ አባላት በጉዳዩ ላይ ተወያይተዋል

 የማኅበረሰቡ አባላት ትናንት በጉዳዩ ላይ በሀዋሳ ከተማ ባካሄዱት ውይይት ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች በማኅበረስቡ አባላት ላይ የግድያ እና መፈናቀል ጥቃት እየፈጸሙ ይገኛሉ ብለዋል። መንግሥት በአካባቢው የሚንቅሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎቸን ትጥቅ እንዲያስፍታ ፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀድሞ ቦታቸው እንዲመልስ እና የሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎችም ካሣ እንዲከፍል ጠይቀዋል። ውይይቱን የተከታተለው የሀዋሳው ዘጋቢያችን ዝርዝሩን ልኮልናል።

ሽዋንግዛው ወጋየሁ